Friday, March 28, 2014

ደብረዘይት ዘቀዳሚት ሰንበት



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 20 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 የነፋሳት ሩጫን ያህል የዓይን ጥቅሻም ያህል ከሰዎችና ከመላእክት ዘንድ በአንድነት ለሚሠገድለት ለእርሱ ምሥጋና ይገባል:: ጥንት በሌለው በፊተኛው፣ ፍጻሜ በሌለው በኋለኛው ስም ሰላም ይሁንላችሁ:: (መጽሐፈ ምሥጢር)

Thursday, March 27, 2014

ደብረዘይት ዘዓርብ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 18 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 ሹመት የእርሱ በሆነ፣ መላእክቱን ለምስጋና በሚያሰልፍ፣ የነፍስ ረቂቅነት ግዙፉ በሆነ፣ ልባችንና ኩላሊታችን በሚታወቅበት፣ ዳግም ለሰው ልጆች የንስሃ ጊዜን በሚሠጥ፣ በደረቀ ሕይወት ዝናሙን በሚያዘንም፣ እውነተኛ የጽድቅ ጎዳና በሆነው በክርስቶስ ስም ሰላም ይሁንልን::

Wednesday, March 26, 2014

ደብረዘይት ዘሐሙስ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 17 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 ጥንት በሌለው፣ ለፊተኛው ፍጻሜ በሌለው፣ አስቀድሞ በነበረ፣ አሳልፎም በሚኖር የእርሱን እስትንፋስ እፍ ብሎ ሕይወት በሰጠን፣ የእርሱን ደም አፍስሶ ዳግም ሰው ባደረገን በልዑል እግዚአብሔር ወልድ ስም ሰላም ይሁንላችሁ::

Tuesday, March 25, 2014

ደብረዘይት ዘረቡዕ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 16 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
                 
 ከሦስትነቱ በማይነጠል፣ የሞቱ በሚነሱም ጊዜ ዳግመኛ ወደ ሥጋ አዳራሽ በሚመልሳት፣ የፀሐይና ጨረቃን አካሄድ ወደ ምዕራብ በሚመልስ፣ የወይራውን ዛፍ በሚነቅለው፣ የተቀጠቀጠውንም ሸምበቆ በሚያጸናው፣ በውጪ ያለውን በሚያስባ፣ በውስጥም ያለውን በሚያስወጣ፣ በእግዚአብሔር ስም በሁሉ ላይ የሠለጠነ ነውና ለእርሱ ምሥጋና ለእናንተም ሠላም ይሁን::

FeedBurner FeedCount