Wednesday, September 26, 2012

መስቀል ኃይላችን ነው



ከጌታችን ስቅለት በፊት መስቀል መቅጫ ነበር፡፡ ሰውን በመስቀል መስቀል የጀመሩት ፋርሳውያን ናቸው፡፡ እነዚህ ሰዎችኦርሙዝድየሚባል የመሬት አምላክ ስለበራቸው እርሱን ላለማርከስ ብለው ወንጀለኛውን ሁሉ ከመሬት ከፍ አድርገው ሰቅለው ይቀጡት ነበር፡፡ በኋላም ይህ አድራጎት በሮማውያን ግዛት ሁሉ ሕግ ሆነ፡፡
በኦሪቱ ሥርዓትም በመስቀል የሚቀጡ ርጉማን ውጉዛን ነበሩ፡፡ ከጌታችን ስቅለት በኋላ ግን የነጻነታችን አርማ የድል ምልክታችን ሆነ፡፡ ክርስቶስ ይህን መስቀል ዙፋኑ አድርጎ ሰላምን እኩልነትን አድርጓልና፡፡ ስለዚህ ካሉን ነገሮች ሁሉ መስቀል የላቀ ክብር አለው፡፡

Monday, September 24, 2012

MESKEL IN ETHIOPIA



In The Name of The Father, The Son; & The Holy Spirit One God Amen!!

The word Meskel has two meanings. One literal meaning is the Holy Cross. The other meaning is the Feast of the Holy Cross; an event which is annually celebrated in Ethiopia in commemoration of the finding of the Holy Cross. The Holy Cross is very significant in the Ethiopian Orthodox Tewahdo Church (EOTC). The founding father of EOTC hymn, St. Yared, says in his composition hymn book ‘MERAF’ that the Holy Cross is above everything else in the Church. He says ‘It saves us from our enemy; the devil. It is true that the Holy Cross has saved the entire world.’

Wednesday, September 19, 2012

ምክረ አበው -ቁጥር ሦስት


1. ከዕለታት በአንድ ቀን አባ ፓምቦ አባ እንጦንስን “ማድረግ ያለብኝ ነገር ምንድነው?” ብሎ ይጠይቋል፡፡ አባ እንጦንስም እንዲህ ሲል መለሰለት “በራስህ ጽድቅ አትታመን፤ ላለፈው አትጨነቅ፤ ይልቁኑ አንደበትህንና ሆድህን ግዛ፡፡”
2. አባ እንጦንስ በአንድ ወቅት እንዲህ አለ፡- “በዚህች ምድር ላይ ስንኖር ሕይወታችንንም ሆነ ሞታችን ከባልንጀራችን ጋር ነው፡፡ ወንድማችንን ገንዘብ ካደረግነው እግዚአብሔርን ገንዘብ እናደርጓለን፤ ወንድማችንን ካስቀየምነው ግን በክርስቶስ ላይ ኃጢአትን እንሠራለን፡፡”

Sunday, September 16, 2012

እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ


  የዮሐንስ ወንጌል 37 ሳምንት ጥናት (ዮሐ.812-20)

     በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

  በምንዝር በያዝዋት ሴት ላይ ለመፍረድ ተሰብስበው የነበሩት አይሁድ ፈሪሳውያን ጌታችን ጸሐፍት ፈሪሳውያን ሆይ! ኃጢአታችሁ ከዚህች ሴት ኃጢአት የባሰ እንደሆነ ተመልከቱ፡፡ ታውቁት ትረዱት ዘንድም አሁን ሕሊናችሁን መርምሩ፡፡ ስለዚህ እናንተው ራሳችሁ ወንጀለኞች ሳላችሁ በዚህች ሴት ላይ የምትፈርዱ አትሁኑ፡፡ ይልቁንም እርሷን ከመውቀሳችሁና ከመክሰሳችሁ በፊት ራሳችሁን የምትወቅሱ ሁኑ፡፡ እርሷ ተወግራ እንድትገደል የምትፈርዱ ከሆነ ግን እናንተም ከዚያ ነጻ አይደላችሁምብሏቸው እነርሱም ይህን ዘለፋ በሰሙ ጊዜ ሕሊናቸው ወቅሷቸው በፊት ከገቡት ጀምሮ በኋላ እስከ ገቡት ድረስ አንድ አንድ እያሉ እየወጡ ሄደው ነበር /.9/፡፡(በዚህ እስ ላይ ይህን ይመልከቱ እኔም አልፈርድብሽም- የዮሐንስ ወንጌል የ36ኛ ሳምንት ጥናት(8፡1-11)

  ሆኖም ግን ተመልሰው መጡ፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ቂመኛ አይደለምና ዳግመኛ አስተማራቸው፡፡ “እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ፤ የሚከተለኝ የሕይወት ብርሃን ይሆንለታል እንጂ በጨለማ አይመላለስም” ብሎ ተናገራቸው /ቁ.12/፡፡ እንዴት ያለ ፍቅር ነው? እንደምን ያለ መውደድ ነው? ፍቁራን ሆይ! የጌታን ንግግር ታስተውሉታላችሁን? እንዲህ ማለቱ ነበር፡-“ፈሪሳውያን ሆይ! እናንተ በመጻሕፍተ ኦሪት የዘለዓለም ሕይወት እንዳለችሁ ይመስላችኋል፤ እነርሱንም ትመረምራላችሁ፡፡ እነርሱ ግን ስለ እኔ የሚመሰክሩ ናቸው /ዮሐ.5፡39/፡፡ እንግዲያውስ ወደ እኔ ኑ እንጂ በዚያ የምትቀሩ አትሁኑ! ዳዊት ‘የሕይወት ምንጭ ከአንተ ዘንድ ነውና በብርሃንህ ብርሃንን እናያለን’ እንዳለ /መዝ.36፡6/ የሕይወት ምንጭ እኔ ነኝና ወደ እኔ ቅረቡ እንጂ በጨለማ የምትቆዩ አትሁኑ፡፡ እውነተኛው ብርሃን እኔ ነኝና ወደ ብርሃን (ወደ እኔ) ኑ! በጨለማ ላለ ሰው ብርሃን ያስፈልጓል፡፡ የተጠማ ሰውም የሚያረካ መጠጥ ያስፈልጓል፡፡ እንግዲያውስ የእነዚህ ምንጫቸው እኔ ነኝና ታገኝዋቸው ዘንድ ወደ እኔ ቅረቡ (በእኔ እመኑ)፡፡ ከእናንተ መካከል አንዱ በሌሊት ውኃ ቢጠማው ተነሥቶ ኩራዝን የማያበራ ማን ነው? ኩራዙንም ተጠቅሞ ውኃ ቀድቶ የሚጠጣ አይደለምን? እንግዲያውስ እናንተም በብርሃኔ ብርሃን የሆንኩትን እኔን ያዙና ዳግመኛ ጽምዓ ነፍሰን የማያስጠማ የሕይወትን ውኃ ጠጡ፡፡ ልጆቼ ሆይ! በጨለማ (በድንቁርና) መኖርን ስለምን ትመርጣላችሁ? እናንተን እንዲሁ አፍቅሬ አማናዊው ብርሃን የምሆን እኔ ወደ እናንተ ስመጣ ስለምን ዐይነ ልቡናችሁን በመዝጋት እኔን ከማየት ትከለከላላችሁ? አባቶቻችሁ ከምድረ ግብጽ ለመውጣት ፊት ለፊት የሚመራቸውን ዓምደ ብርሃንን ተከትለው ከባርነት የወጡ አይደሉምን? /ዘጸ.13፡21/ እንግዲያውስ እናንተም ወደ እውነተኛው ሀገራችሁ (ወደ ገነት መንግሥተ ሰማያት) ለመግባት ብርሃን እኔን ተከተሉ፡፡ እኔ የፍልስጥኤም ወይም የገሊላ ወይም ደግሞ የይሁዳ ብቻ ሳልሆን የዓለም ሁሉ ብርሃን ነኝ፤ የሚከተለኝ(የሚያምንብኝ) ቢኖር የሕይወት ብርሃን ይሆንለታል፡፡ ክብርን፣ ዕውቀትን፣ መንግሥተ ሰማያትን ያገኛል እንጂ በሐሳር፣ በጨለማ ፣ በገሃነም አይመላለስም፡፡ የሚከተለኝ ቢኖር በሴሰኛይቱ ሴት እንዳደረጋችሁት ሳይሆን በራሱ ኃጢአት ላይ ስለሚፈርድ በእኔ አምኖ ይኖራል፡፡ ወደ ክሕደት፣ ወደ ገሃነም፣ በሌሎች ላይ ወደ መፍረድ፣ ወደ ክፉ ነገር አይሄድም፡፡ የሕይወትን ውኃ ክብረ መንግሥተ ሰማያትን ታገኛል፡፡ ስለዚህ በእኔ እመኑና ከስሕተት ከክሕደት ውጡ” /St. Cyril of Alexandria on the Gospel of John, 5:2/፡፡ 

   ፈሪሳውያን ግን ይህን ፍቅር ከመረዳት ራቁ፡፡ መድኅን የሆነው ስሙ ከፍ ከፍ ይበልና አፍቃሪያቸውን እንደ “ዕሩቅ ብእሲ” አይተዉት “የሌለውን አምላክነት” ለራሱ የወሰደ መሰላቸው፡፡ ስለዚህ፡- “አንተ ስለ ራስህ ትመሰክራለህን?” ራስህን የምታመሰግን፣ ራስህንም የምታደንቅ ከሆነማ… አሉት፡፡ ሐሰት የባሕርይው ያይደለ አምላክ “ምስክርነትህ (የምትናገረው ሁሉ) እውነት አይደለም” አሉት /ቁ.13/።  የሚደንቀው ግን

FeedBurner FeedCount