Saturday, March 8, 2014

ምኩራብ ዘሰንበተ ክርስቲያን



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 29 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ

ጸልዩ እምቅድመ ንባበ ዝንቱ ክርታስ

 በነጻነት ልንኖር ክርስቶስ ነጻነት አወጣን፤ እንግዲህ ጸንታችሁ ቁሙ እንደ ገናም በባርነት ቀንበር አትያዙ።”(ገላ 51) በዚህች የክርስቲያን ሰንበት በተባለች ቀን ለሰው ልጆች ሲል በአይሁድ ምኩራብ ለታሰሩት መፈታትን፣ ለባሮች ነጻነትን፣ ለድሆች ፍርድን ሰበከ፡፡ በሚያስደንቅ ትምህርቱ አይሁድ እንኩዋን እስኪደነቁ ድረስ ሰንበታቸውን የጉልበት ሳትሆን የፍቅር፣ ለእነሱ እንጂ እነሱ ለእሷ እንዳልተፈጠሩ አስተማራቸው፡፡ እንግዲህ ይህ ሰላም የተነገረባት የጌታ ቀን በተባለች በዛሬዋ እለት ሰላም ለእናንተ ይሁን፡፡

Friday, March 7, 2014

ቅድስት ዘቀዳሚት ሰንበት


በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 28 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ

ጸልዩ እምቅድመ ንባበ ዝንቱ ክርታስ

 በብሉይ ለሰራት በሐዲስም ለሰው ልጆች ማደሪያውን ያዘጋጅ ዘንድ በመቃብር ባደረባት በቀደመችው ሰንበት ቅዱሱ የእግዚአብሔር ሰው ያሬድ የዚህ ሳምንት ድርሰቱን በፈጸመባት በዚህች ዕለት እርሱ ለቤተክርስቲያን በሚሰጠው ሰላምበሀክሙሰላማውያን ሰላም ያደራችሁ ሰላም ያድርጋችሁ ብዬ ሰላምታዬን ወደ እናንተ ላክሁ፡፡

Thursday, March 6, 2014

ቅድስት ዘዐርብ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 27 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ

ጸልዩ እምቅድመ ንባበ ዝንቱ ክርታስ

 በመስቀሉ ፍቅር ተስባችሁ፣ በሞተ ወልዱ ተቀድሳችሁ፣ በጎኑ ውሃ ፍሳሽነት ታጥባችሁ፣ ለእርሱ የተሰጣችሁ የቅዱሳን ወዳጆች የእናታችሁ ልጆች ሰላምና ፍቅር እናንተን ይክበባችሁ በማለትእለቱን ድርሰት ከአባታችን ጋር እነሆ፡፡

Wednesday, March 5, 2014

ቅድስት ዘሐሙስ


በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ የካቲት 26 ቀን 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ

ጸልዩ እምቅድመ ንባበ ዝንቱ ክርታስ

 ምህረቱን በማንለካው የልብ ጥልቁን በሚያውቀው በብላቴና ድንግል ማህፀን ባደረው የፀሐይ ብርሃን በእርሱ ፊት ጨለማ በሆነ ሰሜንና ደቡብ ምስራቅና ምዕራብ መስዕ እና አዜብ ሳይታወቅ አስቀድሞ በነበረ የፀሐይና የጨረቃን ክበብ እንደ መስታወት በወሰነ ለብርሃናት ጌታቸው በሚሆን በቤተ መቅደሱ በመገናኛው ድንኳን በጥምቀቱ የተወለዳችሁ ሁሉ ከዓለም በሚለየው የጌታ ሰላም ለእናንተ ሰላም ይሁን፡፡ ከኮከብ ለምትበራ፣ ከተራሮች ሁሉ ከፍ ከፍ ላለችው፣ ብርሃኗ የእውነት ፀሐይ ለሆነው ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን በሚያቀርበው ውዳሴ እና የፆምን ነገር ከሊቁ ጋር እያወደስን እየተማርን እንቆያለን፡፡

FeedBurner FeedCount