Thursday, March 20, 2014

መጻጉዕ ዘዓርብ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 11 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 እስከሞት ድረስ በወደደን፤ ስለፍቅር በሞተልን፤ በዚያች ቀን በቀኙ ባለው በኩልዛሬ ከእኔ ጋር ናችሁ” ባለን፤ የእርሱን የምሕረት ቃል ከመስማት የበለጠ ደስታ በሌለን፤ 30 ዘመን ፍቅሩ የሺህ ዘመን ኃጢአታችንን በደመሰሰልን፤ የምሕረቱን ጥልቅነት በሰውኛ ቋንቋችን ልንገልጸው በማንችለው፤ በመስቀሉ ደም ቤዛችን በሆነን፤ ነፃነትና ሰላምን ባጎናጸፈን ሰላም ለእናንተ ይሁን::

Wednesday, March 19, 2014

መጻጉዕ ዘሐሙስ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 10 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 ክርስቶስ አምላኬና ተስፋዬ ነው፤ እፀ መስቀሉም የሐይማኖቴ በትር ነው፤ የጎኑም መወጋት የጥምቀቴ ሻሻቴ፤ የግርፋቶቹም ደም የበለሳን ቅባቴ ነው:: ሐዋርያቱ በመንገዱ የሚመሩኝ ናቸው:: እመቤቴ ማርያም የመድኃኒቴ በር ናት፤ ክንፎቿ በብር የተሠሩ ጎኖቿም በወርቅ ሐመልማል የተሠሩ ነጭ ወፍ (መጽሐፈ ምስጢር):: በሰላማዊቷ ነጭ ወፍ ሰላምታ ሰላም ይሁንላችሁ::

Tuesday, March 18, 2014

መጻጉዕ ዘረቡዕ



በዲ/ን ስመኘው ጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 9 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 በአካል ሦስት፣ በሕልውና አንድ በሆነ፣ በመመርመር ገንዘብ በማያደርጉት፣ ምድራዊውን ዓለም ፈጥሮ በሚገዛ፣ ለመንግስቱ ምሥጋና ሰማያዊን ዓለም በፈጠረ በእግዚአብሔር ስም የቤተመቅደስን ምሥጋና የወንጌልንም ቁርባን ለእርሱ እናቀርባለን:: ጉልበት ሁሉ በሚሰግድለት በአምላክ ስም ሰላም ለእናንተ ይሁን:: (መጽሐፈ ምሥጢር)

Monday, March 17, 2014

መጻጉዕ ዘሠሉስ



በዲ/ንስመኘውጌትዬ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 8 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 በአብና በወልድ በመንፈስ ቅዱሥ ስም፣ አንድ የናዝራውያን አምላክ፣ የማይለወጥ የሃይማኖት ምሰሶ፣ የማይፍገመገም የመርከባችን አለቃ፣ የማይጨልም የፋናችን ብርሃን፣ ከዘመናት አስቀድሞ በህልውና አንድ የሆነ፣ በስምና በስልጣን የሰለጠነ፣ የመለኮቱ አንድነት በማይለወጥ፣ የመንግስቱ ስፋት በማይወሰን፣ የብልጥግናው ክብደት በማይለካ፣ በአንዱ በእርሱ ስም ሰላም ይደረግልን፡፡

FeedBurner FeedCount