Thursday, December 25, 2014

ወደ እግዚአብሔር ለመድረስ (ደረጃ ሦስት)



በዲ/ን ሳምሶን ወርቁ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐሙስ ታኅሳስ 16 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!


“እንደ እንግዳ መኖር”
 የተከበራችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች የመንግሥተ እግዚአብሔር ተጓዦች እንዴት ሰነበታችሁ? እነሆ ሦስተኛውን የመንፈሳዊ ሕይወት ደረጃ በምናባችን ዛሬ እንመለከታለን፡፡ አስቀድመን የመጀመሪያውን የመንፈሳዊ ሕይወት ደረጃ ጀርባችንን ለዓለም በመስጠት ጀምረናል፡፡ በመንገዱ ያሰበበት ለመድስ የሚጓዝ አሽከርካሪ በመንገድ እንዳይቀር በየደረሰበት ከተማ ነዳጅ እንደሚሞላ እኛም ተስፋ ወደምናደርጋት መንግሥተ እግዚአብሔር እስክንደርስ ድረስ በየደረጃዎቹ ላይ የምናገኛቸውን የቃለ እግዚአብሔር ስንቅ እየቋጠርን እንጓዛለን፡፡ በባለፈው ጽሑፍ “ከዓለማዊ መሻት መለየት” ሁለተኛውን የመንፈሳዊ ሕይወት ደረጃ ተመልክተናል፡፡ ከዓለማዊ መሻት መለየት በዓለም ካለው አላፊ ጠፊ ከሆነው ከገንዘብ ከሥልጣን ከዕውቀት ፍቅር ተለይተን፤ በምድር ላይ ስንኖር አለን የምንለው ነገር ሁሉ ከእኛ እንዳልሆነ አውቀን፤ ከራስ ወዳድነት ርቀንና ከውዳሴ ከንቱ ተለይተን መኖር ማለት መሆኑን ተመልክተናል፡፡

Tuesday, December 23, 2014

ትምህርተ ሃይማኖት (ክፍል ስድስት)



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ማግሰኞ ታኅሳስ 14 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!


መ) ዶግማ እና ቀኖና
 ውድ የመቅረዝ ተከታታዮች! እንዴት አላችኁ? ትምህርተ ሃይማኖት በሚል ርእስ መማማር ከዠመርን የዛሬ ስድስተኛው ክፍል ነው፡፡ ባለፉት አምስት ተከታታይ ትምህርቶች የሃይማኖት ትርጕም፣ ሃይማኖት ያላቸው ፍጥረታት፣ የሃይማኖት አስፈላጊነት፣ ኦርቶዶክስና ተዋሕዶ ስለሚሉ አገላለጾች፣ ስለ ነገረ ቤተ ክርስቲያን፣ ስለ ቅዱስ ትውፊት እንዲኹም ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ኦርቶዶክሳዊ አረዳድ ተመልክተናል፡፡ ለዛሬ ደግሞ ከመግቢያው የመጨረሻ ስለኾነው ስለ ዶግማና ቀኖና እንማማራለን፡፡ ቢቻላችኁ ለማንበብ በቂ ጊዜ ሰጥታችኁና ተረጋግታችኁ ብታነቡት መልካም ነው፡፡ እግዚአብሔር ዓይነ ልቡናችንን ያብራልን፡፡ አሜን!!!

Friday, December 19, 2014

የንስሐ ልጆቼን እንዴት ላገልግል? (የመጨረሻው ክፍል)

በዳዊት አብርሃም
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ቅዳሜ ታኅሳስ 11 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
የጽሑፉ ምንጭ፡- ሐመር መጽሔት፥ የግንቦት 2005 ዓ.ም. እትም ነው፡፡
ኃጢአትን በመናዘዝ ውስጥ የሚገኝ ፈውስ
ከኃጢአት እስራት በንስሐ ለመፈታት ፈልጐ ወደ ካህኑ የሚቀርብ ተነሳሒ የሚታይበትና ከዚያም በሒደት አልፎበት በመጨረሻ የሚደርስበት የመንፈስና የሥነ ልቡና ኹኔታ አለ፡፡ ይኽንን ኹኔታ ቀሲስ ፋሲል ታደሰ እንደሚከተለው ይገልፁታል፡፡
ደረጃ አንድ
ተነሳሒው ለመዠመሪያ ጊዜ ሲመጣ የተረበሸ ኹኔታ ፊቱ ላይ ይነበባል፡፡ ቁጣ ቁጣ የሚለው የዘለፋና ወቀሳ የሚያበዛ ለራሱ የሰጠውን ዝቅተኛ ግምትና ውስጡ ያደረውን ታላቅ ተስፋ መቁረጥ ቁልጭ አድርገው የሚያሳዩ ኹኔታዎች ከገጽታው ይነበባል፤ ካንደበቱ ይደመጣል፡፡

Wednesday, December 17, 2014

የንስሐ ልጆቼን እንዴት ላገልግል? (4)

በዳዊት አብርሃም
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐሙስ ታኅሳስ 9 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
የጽሑፉ ምንጭ፡- ሐመር መጽሔት፥ የግንቦት 2005 ዓ.ም. እትም ነው፡፡
መንፈሳዊ ቤተ ሰብ
ቀሲስ ጥላኹን ታደሰ 110 ያኽል የንስሐ ልጆቻቸውን በጥንቃቄ መዝግበው ይዘዋል፡፡ ይኽም እያንዳንዱ የንስሐ ልጅ ያለበትን ደረጃ ለመከታተል አስችሏዋቸዋል፡፡ ከመዠመሪያው የንስሐ ልጆቻቸውን ለመቀበል መንፈሳዊ መስፈርቶችን በቅድመ ኹኔታነት ያስቀምጣሉ፡፡ በመዠመሪያ ግን የሚያቀርቡት ጥያቄ “ለምን የንስሐ አባት አስፈለገህ?” የሚል ነው፡፡ ይኽን ጥያቄ የሚያነሡት እያንዳንዱ የንስሐ ልጅ ትክክለኛውን ዓላማ ይዞ የንስሐ ሕይወቱን እንዲዠምር ለማድረግ ነው፡፡ ቀጥለው መስፈርቶቹን ይነግሩታል፡፡ ተስማምቶ ቢቀጥል እንኳ በየጊዜው ለመፈጸም የተስማማባቸውን መስፈርቶች በትክክል እየፈጸመ መኾኑን ከመመርመር አያቆሙም፡፡

FeedBurner FeedCount