Thursday, August 9, 2012

ከሕዝቡ ግን ብዙዎች አመኑበት- የዮሐንስ ወንጌል የ34ኛ ሳምንት ጥናት


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

  ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ካላቸው እይታ አንጻር የሥነ መለኰት ምሁራን አይሁድን በሦስት ምድብ ይመብዋቸዋል፡፡ አንደኛው ምድብ የአለቆች፣ የካህናትና የፈሪሳውያን ምድብ ሲሆኑ እነርሱም ለክርስቶስ ፍጹም ጥላቻ የነበራቸው ናቸው፡፡ ሁለተኛው ምድብ ደግሞ በኢየሩሳሌም ውስጥ የሚኖሩና በአንደኛው ምድብ ባየናቸው ቡድኖች ጥላቻ ግራ የተጋቡ ናቸው፡፡ እነዚህ ሰዎች የአለቆቻቸውን ጥላቻ ቢያውቁም ጌታ በሚያደርጋቸው ገቢረ ተአምራት ፍጹም የሚማረኩ ናቸው፡፡ ጌታን ለአለቆቻቸው አሳልፈው እንዳይሰጡት በሚያስተምራቸው ትምህርት፣ በሚያሳያቸው ፍቅር፣ በሚያደርግላቸው ምልክት ልባቸው የተወሰዱ ናቸው፡፡ ሦስተኛው ምድብ ደግሞ ከኢየሩሳሌም ውጪ የሚኖሩ ናቸው፡፡ እነዚህ ከኢየሩሳሌም ውጪ የሚኖሩ አይሁዳውያን ለገቢረ በዓል ወደ ኢየሩሳሌም ሲመጡ በክርስቶስ እጅግ የተማረኩና በምድብ አንድ ያየናቸውን አለቆች ስሜት የማያውቁ ናቸው፡፡ እነዚህ ሰዎች አለቆች ክርስቶስን ሊገድሉት እንደሚፈልጉ ሲሰሙ በእጅጉ የተደናገጡና በአለቆቹ ክፉ ሥራ ግርምት ውስጥ የገቡ ናቸው /Fr.Tadros Malaty,Commentary on the Gospel of John,pp359/፡፡

  አሁን ወንጌላዊው እየነገረን ያለው የሁለተኛው ምድብ የሆኑ ሰዎች ስሜት ነው፡፡ “እንግዲህ ከኢየሩሳሌም ሰዎች አንዳንዶቹ እንዲህ አሉ፡- ሊገድሉት የሚፈልጉት ይህ አይደለምን? እነሆም፥ በግልጥ ይናገራል አንዳችም አይሉትም። አለቆቹ ይህ ሰው በእውነት ክርስቶስ እንደ ሆነ በእውነት አወቁን? ነገር ግን ይህን ከወዴት እንደ ሆነ አውቀናል፤ ክርስቶስ ሲመጣ ግን ከወዴት እንደ ሆነ ማንም አያውቅም” እንዲል /ቁ.25-27/። እንዲህ ማለታቸው ነበር፡-“አለቆቻችን እንገድለዋለን ብለው የሚዝቱበት ይህ አሁን በድብቅ ያይደለ በይፋ በስውር ያይደለ በግልጥ የሚያስተምራቸው አይደለምን? እነሆ፡- ከእናንተ ሕግን የሚያደርግ አንድ ስንኳ የለም ብሎ በግልጥ ይናገራል /ቁ.19/፤ ሆኖም ግን አንዳች ስንኳ አይሉትም፡፡ ወይስ ይህ ሰው በእውነት ክርስቶስ እንደሆነ አውቀዋል ማለት ነው? ይህ አሁን የሚናገረው ሰውዬ (ሎቱ ስብሐትና) ከቤተ ልሔም እንደተወለደ የቀራጩ የዮሴፍም ልጅ እንደሆነ እናውቃለን /ማቴ.2፡4/፡፡ ክርስቶስ ሲመጣ ግን ኢሳይያስ፡- ትውልዱን ማን ይናገራል ብሎ እንደተናገረ ማንም አያውቅም” /ኢሳ.53፡8፣ Saint Cyril the Great/፡፡

 የእነዚህ ሰዎች ችግር ነቢዩ ኢሳይያስ የተናገረው ቃል ለቀዳማዊ ልደቱ ከማድረግ ይልቅ ለደኃራዊ ልደቱ አድርገው መረዳታቸው ነው፡፡ ነቢያቱ ግን እንዲህ የቀዳማዊ ልደቱ አይመረመሬነት እንደተናገሩ ሁሉ /ኢሳ.53፡8/ ሰው ሆኖ ከድንግል እንደሚወለድም በግልጽ ቦታውን ሳይቀር ጨምረው ተናግረዋል /ኢሳ.7፡14፣ ሚክ.5፡2/፡፡

   ከዚህ በኋላ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመቅደስ ሲያስተምር፡-እኔንም ታውቁኛላችሁ ከወዴትም እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ፤ እኔም በራሴ አልመጣሁም ነገር ግን እናንተ የማታውቁት የላከኝ እውነተኛ ነው፤ እኔ ግን ከእርሱ ዘንድ ነኝ እርሱም ልኮኛልና አውቀዋለሁ” ብሎ ጮኸ /ቁ.28-29/። እንዲህ ማለቱ ነበር፡- “ጀሮ ያለው መስማትን ይስማ፤ ነቢያት አብዝተው እንደነገሯችሁ ከወዴት እንደሆንኩ (ናዝሬት ገሊላ እንዳደግኩ)፣ ከወዴት እንደተወለድኩ (ከቤተልሔም እንደተወለድኩ)፣ ከማን ወገን እንደተወለድኩ (ከዳዊት ወገን እንደተወለድኩ) ታውቃላችሁ፡፡ ሆኖም ግን ከአብ ባሕርይ ዘእምባሕርይ አካል ዘእምአካል የተወለድኩትን ቀዳማዊ ልደቴን ጨምረው የነገርዋችሁን አታውቁም ብዬ በእውነት እነግራችኋለሁ፤ ይህን ከማመን ይህን ከመቀበል በፍቃዳችሁ ተከልክላችኋል ብዬ በእውነት ያለ ሐሰት እነግራችኋለሁ/St. John Chrysostom, Hom 50./፡፡ በእኔ ፈቃድ ብቻ ያይደለ በበአባቴም ፈቃድ ሰው ሆኛለሁና እርሱን ብታምኑበት እኔም ከእውነት የተወለድኩ እውነት እንደሆንኩ ባወቃችሁ ባመናችሁ ነበር፡፡ ደጋግሜ እንደነገርኳችሁ እኔ በህልውና ያየሁትን ነገርኳችሁ እንጂ አብን በባሕርይው ያየው አንድ ስንኳ የለም /ዮሐ.1፡18/፡፡ እኔ ልገልጽለት ያልፈቀደ፣ በእኔ ያላመነ ሁሉ አብን ሊያየው ሊያውቀው የሚችል እንደሌለ በእውነት እነግራችኋለሁ፤ ወልድን ያየ ግን አብን አይቷል ብዬ በእውነት ያለ ሐሰት እነግራችኋለሁ” /ዮሐ.14፡9፣ Augustine, On the Gospel of St. John, tractate 31/፡፡  

  ፈሪሳውያን ግን እንዲህ ስለተናገረ ሊይዙት ይፈልጉ ነበር፤ ከማር በሚጣፍጠው መለኰታዊ ቃሉ የሕዝቡን ልብ እንደወሰደ ወደ እውነትም እንደመለሰ ሲያውቁ ሊገድሉት ይፈልጉ ነበር፡፡ ነገር ግን ጊዜው ገና ስላልደረሰ የሚሰቀልበት ሰዓት ስላልደረሰ በመለኰታዊ ሥልጣኑ ይህን እንዳያደርጉ ከለከላቸው፤ ስለዚህ ማንም እጁን አልጫነበትም /ቁ.30/።

  የፈሪሳውያን ቁጣ እየበዛ በሄደ ቁጥር ሕዝቡም እውነቱን እየተረዳ እያወቀ መጣ፡፡ ነገር ሁሉ ግልጽ እየሆነለት መጣ፡፡ ስለዚህ ከሕዝቡ ብዙዎች አመኑበት፡፡ ያመኑትም ሕዝብ እንዲህ ብለው ተነጋገሩ፡-አይሆንም አይደረግም እንጂ አለቆቻችን ይመጣል ብለው የሚነግሩን ክርስቶስ በመጣ ጊዜ ይህ አሁን ያመንንበት ክርስቶስ ካደረጋቸው ምልክቶች በላይ ተአምራትን ያደርጋልን?” /ቁ.31/፡፡ የሚደንቅ ነው! ሕሙማነ ሥጋ በተአምራት ሕሙማነ ነፍስም በትምህርት ሲፈውሳቸው በዙርያ የነበሩ ድሆች አመንዝሮችና ቀራጮች አመኑበት፡፡ እናውቃለን ከሚሉት እረኞች ይልቅ የተበደሉት ሰዎች ዳኑበት፡፡ ቁስላቸውን ፈወሱበት፡፡ ስብራታቸውን ጠገኑበት፡፡ ተስፋቸውን ቀጠሉበት፡፡ ከውድቀታቸው ተነሡበት፡፡ አለቆች ነን ባዮቹ ግን አንዳችም ሳይጠቀሙ ከነደዌአቸው ቀሩ፤ ወደ ሐኪማቸው ከመቅረብ ተከለከሉ፤ ይባስ ብለውም ሊገድሉት ፈለጉ፡፡
  ሕዝቡ ሰለ ክርስቶስ እንደዚህ ሲነጋገሩ ሲሰሙም ሎሌዎቻቸውን ላኩ /ቁ.32/። ሰው ወዳጁ ጌታ … ሰው አፍቃሪው ንጉሥ ግን እንዲህ አላቸው፡-“ፈሪሳውያን ሆይ! በዚህ ዓለም ከእናንተ ጋር ብዙ እንደምቆይ ስለምን ትቆጣላችሁ? ሸክም እንደሆንኩባችሁ አውቃለሁ፡፡ ክፋታችሁን በእውነት ስለምናገርባችሁ አውቃለሁ፡፡ ሰላም እንደነሣኋችሁ አውቃለሁ፡፡ ሆኖም ግን እኔ ሳልፈቅድላችሁ ማድረግ አትችሉምና ጊዜዬ ሳይደርስ እኔን ለመግደል በከንቱ የምትደክሙ አትሁኑ፡፡ በቅናትና በቁጣ ተነሳሥታችሁ እኔን ለመግደል የምትቻኮሉ አትሁኑ፡፡ ድኅነተ ዓለም የምፈጽምባትን የእኔን ሰዓት፣ በእኔ ዘላለማዊ ዕቅድ ውስጥ ያለችውና መከራ መስቀልን የምቀበልባት ያቺ ሰዓት ስትደርስ በፈቃዴ፣ ወድጄ ራሴን እሰጣችኋለሁ፡፡ ከዚያን ጊዜ በኋላ ግን ሥራችሁ ክፉ ነውና ፈጽሞ አታገኙኝም፤ በጨለማ መኖርን የምትወዱ ናችሁና ወደ ብርሃን መውጣት የማትፈልጉ ናችሁና ስለዚሁ በእናንተ ዘንድ የማድር የምዋሐድ አይደለሁምና አታገኙኝም፡፡ አንድም ጥጦስ መከራ ሲያደርስባችሁ ትሹኛችሁ፤ አታገኙኝም፡፡ አንድም ጻድቃንን ልፈርድላቸው ኃጥአንን ልፈርድባቸው በመጣሁ ጊዜ አምነንበት ቢሆን ብላችሁ ትፈልግኛላቹ፤ አታገኙኝም፡፡ መንገዱም እውነቱም እኔ ነኝና በእኔ ሳታምኑ ተድላ ደስታ ወዳለባት መንግሥተ ሰማያት መምጣት አይቻላችሁምና አታገኙኝም፡፡ ፈሪሳውያን ሆይ! ጥቅም በሌለው ምክር ራሳችሁን የምታጎሳቁሉ አትሁኑ፡፡ አለቆች ሆይ! መከራ ነፍስ የሚያመጣባችሁ ነውና ቁጣችሁን ወደ ሰገባው መልሱት፡፡ በተወደደ ሰዓት ሰማሁህ በመዳንም ቀን ረዳሁህ ይላልና እነሆ የተወደደ ሰዓት አሁን ነው፤ እነሆ የመዳን ቀን አሁን ነው /2ቆሮ.6:2/፡፡ አትሳቱ! ሰው የሚዘራውን ሁሉ ያንኑ ደግሞ ያጭዳልና የዘለዓለምን ሕይወት ታጭዱ ዘንድ በመንፈስ የምትዘሩ ሁኑ /ገላ.6፡7-8/፤ በእኔ እመኑ በአባቴም እመኑ፡፡ እኔስ ሞታችሁን እገድል ዘንድ እናውቀዋለን ከምትሉት ሆኖም ግን ከማታውቁት ከአባቴ ዘንድ መጥቻለሁና፣ ሕይወት ይሆንላቸው ዘንድ ለወደዱ ሕይወትን እሰጣቸው ዘንድ ሰው ሆኛለሁና ሞት በእኔ ላይ ሥልጣን የለውም፡፡ ሰዓቱ ሲደርስ ግን የሲዖል የምሥጢር በሮችን እሰባብራለሁ፡፡ ምርኮን እማርካለሁ፡፡ ስለዚህ እናንተ እንደምታስቡት ፈጥነንም እናስወግደው እንደምትሉት በመቃብር በስብሼ የምቀር አይደለሁም፡፡ ከሙታን ተለይቼ እነሣለሁ እንጂ፡፡ መነሣትም ብቻ ሳይሆን ደቀመዛሙርቴ እያዩኝ በይባቤ መላዕክት በቅዳሴ በብርሃን በሥልጣን ዐርጋለሁ /መዝ.46፡5/፡፡ ያኔ ሰዎች ዕርገቴን አይተው ያደንቃሉ፤ መላእክትም፡-“ይህ በእጅህ መካከል ያለ ቁስል ምንድነው?” ይሉኛል፤ እኔም “በወዳጆቼ ቤት የቆሰልኩት ቁስል ነው” እላቸዋለሁ /ቁ.33-34፣ ዘካ.13፡6፣ St. Augustine: On the Gospel of St. John, tractate 31:9/፡፡

  ከዚህ በኋላ አይሁድ፡-እኛ እንዳናገኘው ይህ ወዴት ይሄድ ዘንድ አለው? በግሪክ ሰዎች መካከል ተበትነው ወደሚኖሩት ሊሄድና የግሪክን ሰዎች ሊያስተምር አለውን? እርሱ። ትፈልጉኛላችሁ አታገኙኝምም እኔም ወዳለሁበት እናንተ ልትመጡ አትችሉም የሚለው ይህ ቃል ምንድር ነው?” ብለው እርስ በርሳቸው ተነጋገሩ /ቁ.35-36/።

  ቸርነትህ የበዛ አፍቃሪያችን ሆይ! በመንግሥትህ በመጣህ ጊዜ አስበን፡፡ ቀን ሳለልን በብርሃን እንድንመላለስ እርዳን፡፡ ዓለምን ለማሳለፍ በመጣህ ጊዜ ያ የቀመስነውና የለመድነው የፍቅር ፊትህ በምግባራችን ክፋት እንዳይለወጥብን ዛሬ ላይ በምግባር በትሩፋት እንድንመላለስ እርዳን፡፡ ሙሽራችን ሆይ! ዘይታችን አልቆ ከውጭ ከሚቀሩ ቆነጃጅት እንዳንሆን ደግፈን፡፡ የአባቴ ብሩካን ከምትላቸው ወዳጆችህ ጋር ደምረን፡፡ አሜን በእውነት አሜን!!!!!!!

Wednesday, August 8, 2012

የምክር ቃል ከቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ!


 ክርስቶስን ትለብስ ዘንድ በውኃ ስሙን እየጠራህ ተጠምቀሃል፡፡ በጥምቀትም የጌታህ ዙፋን አካልህ እንደሆነ ማኅተሙም በግንባርህ ላይ እንደታተመ ልብ በል፡፡ ከእንግዲህ አንተ የሌሎች ሌሎችም የአንተ ጌቶች አይደሉም የጌታ እንጂ፡፡
በርህራሄው ዳግም የፈጠረን ጌታ ኢየሱስ አንድ ነው፡፡ በመስቀሉ ላይ በፈፀመው ቤዛነት በኩል እኛን ያዳነን እርሱ አንድ ነው፡፡ ሕይወታችንን በጽድቅ የሚመራት እርሱ ብቻ ነው፡፡ ትንሣኤያችንን የሚፈጽምልን እርሱ ነው፡፡ እንደ ሥራችንም ዋጋችንን የሚከፍለን እርሱ ነው፡፡ በሥራዎቹ ቸርና ሩህሩህ የሆነውን አባት እንዳታስቆጣው፡፡
በባልንጀራህ ላይ የምትቆጣ ከሆነ የአንተ ቁጣ በእግዚአብሔር ላይ ነው፡፡ በባልንጀራህ ላይ ቂምን በልብህ የያዝክ ከሆነ ቂምህ በጌታ ላይ ነው፡፡ ባልንጀራህን በከንቱ የምትቆጣው ከሆነ ኃጢአት በአንተ ላይ ይስለጠንብሃል፡፡ ልብህን የፍቅር ማደሪያ ካደረከው በምድር ላይ አንዳች ጠላት አይኖርህም፡፡
አምላክህ ክርስቶስ ስለ ገዳዮቹ በመስቀሉ ላይ ሳለ ይቅርታን ለመነ፡፡ እንዴት አንተ ፍጥረትህ ከትቢያ የሆነ ቁጣን በፈቃድህ በራስህ ላይ ታቀጣጥላለህ? አንተ በክርስቶስ ደም ወደ እርሱ ቀርበሃል፤ በሕመሙም ድነሃል፡፡ በአንተ ፈንታ ለኃጢአት ስራዎችህ ምትክ ሆኖ ስለ አንተ መተላለፍ እርሱ ሞቷል፡፡ አይሁድ በመዘበት በፊቱ ላይ ምራቃቸውን ሲተፉበት መታገሱ ሰዎች ቢያፌዙብህ እንኳ እንድትታገሳቸው አርአያ ሊሆንህ ነው፡፡ መራራና ሆምጣጣ የሆነውን ወይን መጎንጨቱ ከቁጣ ትሸሽ ዘንድ ነው፡፡ በጅራፍ ተገርፎ፣ በሰንሰለት ታስሮ መጎተቱ ስለ ጽድቅ ስትል መከራን እንድትቀበል ነው፡፡ 
(ምንጭ፡- ስብከት ወተግሳጽ ዘቅዱስ ኤፍሬም፣ በመ/ር ሽመልስ መርጊያ፣ ገጽ 65-66)

ፍቕሪ እግዚኣብሄርስ…

ሓደ ሓደ ሰባት ኣዳም ካብ ገነት ብምብራሩ ከም ቅፅዓት ጥራሕ ገይሮም ይሓስብዎ፡፡ ኣቦና ቅዱስ ኤፍሬም ወዲ ሶርያ ግና፡- “አዳም ካብ ኤደን ገነት ዝወፅአስ ብፍቕሪ ኣምላኽ እውን ደኣ ‘ምበር በቲ ቕኑዕ ፍርዲ ኣምላኽ ጥራሕ ኣይነበረን” ይብለና፡፡ “ከመይሲ ኣዳም ምስ ኣበሰ ካብ ገነት እንተዘይባረር ነይሩ ምስ ርስሓቱ እንዳሃለወ እታ ናይ ሂወት ኦም ምበልዐ ነበረ፡፡ እዚኣ በልዐ ማለት ከዓ ካብ ርስሓቱ እንተይፀረየ ማለት እውን ምስ ጉድለቱ እንዳሃለወ ናብ መንግሥተ ሰማይ ምኣተወ ነይሩ፡፡ ንዘላኣለም እውን ጐዶሎ ምኾነ ነበረ፡፡ ኮይኑ ግና ጐይታ ኣፅርዩ ከእትዎ ስለ ዝደለየ ክሳብ ባዕሉ መፂኡ ዘፅርዮ በቲ ቅኑዕ ፍትሑ ካብ ገነት አውፅኦ፡፡ ጊዜኡ ምስ በፅሐ ውን ባዕሉ መፂኡ ሥጋኡን ደሙን ናይ ሂወት ኦም ገይሩ ሃቦ’ሞ ነቲ ብልቡ ዝሐዘነ ኣዳም ናብ ናይ ቀደም መንበሪኡ መለሶ” ይብለና!!
እሞ እቲ ፍቕሪ እግዚአብሔርስ ዋላ ኣብቲ ንዓና ሕማቕ ዝመስለና ሃዋህው እውን ምህላዉ ኣየግርምን ዶ ትብሉ?

Tuesday, August 7, 2012

KADHATA


   
Maqaa Abbaa kan Ilmaa kan Afuura Qulqulluu Waaqa Tokko Ameen!
SEENSA
   Kadhata jechuun harka Waaqayyoo irraa eebba gaafachuu jechuu dha. Karaa kan birootiin immoo gatii kadhannaadhaan argamu jechuu dha. Kanaafis ragaan “Isa kadhateef gatiin isaa isaaf laatama” jedha. Gabaabaatti kadhata jechuun Waaqayyo wajjin haasa’u meeshaa wanna feene (barbaanne) tokko Waaqayyo biraa ittiin argannu dha. 
  Kadhata yeroo mara osoo addaan hin kutiin kadhachuun akka nurra jiru; addaan kutuun akka nurra hin jirre yeroo barsiisu Gooftaan fakkeenyaan akkas jedhee isaanitti dubbate kunis Wangeela Luqaas boqonnaa 18 lakk. 1-14 irratti isa barreeffame dha. Kadhannaadhaaf gaggeessaa keenya kan ta’e Gooftaan keenya Iyyesuus Kiristoos iddoo tokkotti kadhannaa taasisee erga xumuree booda barattoota (duukaa buutota) isaa kessaa tokko “Yaa Gooftaa Yohaannis barattoota isaa akkuma kadhannaa barsiise; atis nuun nu barsiisi” isaan jedhe. Gooftaan keenyas deebisee isinis yeroo kadhattan; “Yaa Abbaa keenyaa samii irra kan jiraattu maqaan kee haa galateeffamu; mootummaan kee haa dhufu eeyyamni kee samii irratti akkuma ta’e akkasumas lafa irratti haa ta’u kan nu ga’u soorata keenya (biddeena keenya) har’a nuuf laadhu (kenni) kan nu yakkaniif yakka isaanii akkuma dhiisnu yakka keenya nuuf dhiisi hamaa irraa nu oolchi malee qorumsatti nu hin galchiin.” (Luq. 11: 1-4) jedhee isaan  barsiise. 
  Kanaafuu kiristaana kan ta’e martinuu maqaa Abbaa Ilmaa Afuura Qulqulluutti amanee qaamolee sadan waaqummaadhaan waaqa tokko jedhee yeroo mara kadhannaa gara Uumaa isaatti dhiyeessuu qaba. Kadhannaan abboommii Waaqa biraa ajajame ta’uun isaa kitaaba qulqulluu keessatti iddoo baay’eetti barreeffameera. 
1ffaa - Gooftaan keenyaa fi Fayyisaan kenyaa Iyyesuus Kiristoos  “Qormaatatti akka hin seenneef jabaadhaa kadhadhaa” jedheera. (Maat.26:41)
2ffaa – “Kan kadhattan mara akka argattaniitti taasisaa amanaa isiniif raawwatama. Kadhannaadhaaf yeroo dhaabbattanus Abbaan keessan inni samii gubbaa jiraatu ammoo cubbuu keessan akka isinii dhiisuuf eenyu illee kan isin yakke yoo jiraate dhiifama godhaafi dhiifama gochuufii yoo diddan Abbaan keessanis dhiifama isiniif hin godhu. (Maar. 11:24-26) 
3ffaa – “Onneen keessan baay’ina dhugaatii fi machiin waa’ee gaa’ilaa yaaduun akka hin dadhabne, guyyaan sunis akka tasaa akka isinitti kiyyoo isinirraan ga’u egaa dhufuuf kan jiru kana mara  jalaa miliquuf ilma namaa (Kiristoos) dura dhaabbachuuf akka dandeessanitti yeroo kadhattanu yeroo mara jabaadhaa. (Luq. 21:34-36)
4ffaa – “Dhuguma dhuguman isiniin jedha; Abbaan maqaa kootiin kan isin kadhattanu mara isiniif laata (kenna) hanga yoonaatti maqaa kootiin homaa hin kadhanne gammachuun keessan tasa gaarii akka ta’uuf kadhadhaa ni fudhattu.” (Yoh. 16:24) Duukaa bu’ichi fi Qulqullichi Phaawuloosis “Osoo addaan hin kutiin kadhadhaa” isan jedhe sanas hin dagatiin (1 Tasaloonqee 5:16)
  Egaa gabaabaadhumatti seensa kadhannaaf akka ta’u yaadnee kan barreessine kun kadhannaa isa guddaaf seensa akka ta’uuf yaadnee kadhannaa isa guddaa irraa hir’isnee gabaabsuudhaan Afaan Gi’iiziitiin isa barreeffame mara amantoota Afaan Gi’iizii fi Afaan Amaaraa hin beekneef Afaan Oromoo isa beekaniin yoo kadhatan akkan isaan fayyadu ta’uu isaa yaaduun yeroo mara sa’aatiitiin kadhachuu kan danda’an martinu akka ittiin kadhatanuuf sababa hojiitiin yeroo yerootti kadhachuu namoota hin dandeenyeef sa’aatii mijataa guyyaa boqonnaa akka ittiin kadhatanuuf yeroo gabaabaa keessatti  dubbisamee kan dhumu baay’atee kan hin quufamne kitaaba jaallatamaa waan ta’eef amantoonni martinuu akka itti fayyadamanuuf kitaabni kun qophaa’eera. 
Itti fufa...   
Galanni Waaqayyoof akkasumas Haadhaa fi Giiftii keenya Maariyaamiif haa ta’u Ameen!
( Qopheessaan: Nugusuu Alamuu)

FeedBurner FeedCount