Monday, September 15, 2014

የትምህርተ ሃይማኖት መግቢያ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መስከረም 5 ቀን፣ 2007 ..)- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
 “ሃይማኖትማለት አምነ፣ አመነ ከሚል የግእዝ ግሥ የወጣ ሲኾን መዝገበ ቃላታዊ ትርጓሜውምማመን፣ መታመንማለት ነው፡፡ በምሥጢራዊው ትርጕሙ ግንሃይማኖትማለት ፍጥረትን ኹሉ ካለ መኖር ወደ መኖር ያመጣ አንድ እግዚአብሔር እንዳለ፣ ለሚታየውም ለማይታየውም ፍጥረት ሠራዒውና መጋቢው ርሱ ብቻ እንደኾነ፣ ልዩ ሦስትነት እንዳለው፣ በዚኽ አለ በዚኽ የለም የማይባል ምሉዕ በኵለሄ እንደኾነ፣ማመን መታመን ማለት ነው፡፡

Tuesday, September 9, 2014

ዘመኔን አድሰው


በወርቅነሽ ቱፋ
ይኸው
ሩቅ ያልኩት ቀረበ፥ ነገ ዛሬ ሊኾን፥ መጣ እየበረረ፤
በለስ ሕይወቴም ሲፈተሸ፥ ምንም አላፈራ፥ አላዘረዘረ፡፡

Sunday, September 7, 2014

አዲሱ ዓመት - ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዳስተማረው (የመጨረሻው ክፍል - ክፍል ፬)



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ጳጉሜ ፪ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
የቀጠለ…
 እግዚአብሔር የሚወዳችኁ እናንተም የሚምትወዱት ልጆቼ! ይኽን ኹሉ በዝርዝር የምነግራችኁ ለምን ይመስላችኋል? ይኽን ኹሉ በዝርዝር መናገሬ በዘዴ ኹላችንም የምናደርገውን ማናቸውም እንቅስቃሴያችን ለእግዚአብሔር ክብር እናደርገው ዘንድ ስለምሻ ነው፡፡ በባሕር የሚነግዱ ነጋዴዎች ንብረታቸውን ወደ ከተማ ዳር መልሕቅ ካመጡ በኋላ መዠመሪያ የሚያደርጉት ነገር ቢኖር በቀጥታ ወደ ገበያ ሥፍራ መሔድ አይደለም፡፡ ወደ ገበያ ሥፍራ ከመሔዳቸው በፊት ስለ ትርፋቸው ያስባሉ እንጂ፡፡ እኛም በምናደርገው ኹሉ ከእግዚአብሔር ዘንድ የምናገኘውን ጥቅም ማሰብ አለብን፡፡

Saturday, September 6, 2014

አዲሱ ዓመት - ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዳስተማረው (ክፍል ፫)



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ጳጉሜ ፩ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
የቀጠለ…                       
 ለእግዚአብሔር ክብር ብሎ ሰውን መውቀስም አለ፡፡ ከእናንተ መካከል፡- “እንዴት ብሎ? ርግጥ ነው ብዙውን ጊዜ ሠራተኞቻችንን እንወቅሳለን፡፡ ለእግዚአብሔር ክብር ብሎ መውቀስስ እንደምን ያለ ነው?” አዎ! የሚሰክር ወይም የሚሰርቅ ሠራተኛ ወይም ጓደኛ ብናይ ወይም ከዘመዳችን አንዱ ወደ ተውኔት ቤት፣ ወይም ለነፍሱ ምንም ረብሕ ወደማያገኝበት ሥፍራ ሲሮጥ፣ በከንቱ ሲምል፣ የሐሰት ምስክርነትን ሲሰጥ፣ ወይም ሲዋሽ፣ ወይም ሲቈጣ ብናየው ዠርባችንን ብንሰጠውና ብንገሥፀው ወቀሳችን ለእግዚአብሔር ክብር የተደረገ ነው ይባላል፡፡

Tuesday, September 2, 2014

አዲሱ ዓመት - ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዳስተማረው (ክፍል ፪)




(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ነሐሴ ፳፯ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
የቀጠለ…

 ከገቢረ ኀጢአት ሳይወጡ አዲስ ዓመት ሲመጣ መደሰት፣ ብዙ መብልና መጠጥ ማዘጋጀት፣ አዲስ ልብስም መልበስ ጥቅም የለውም፡፡ ነፍሳችን በኀጢአት እየተጨነቀች፣ ነፍሳችን ተርባና ተጠምታ ሳለ፣ የተዳደፈ የኀጢአት ልብስም ተጆቡና ሳለ አዲስ ዓመት ማክበር ለእኛ ምን ጥቅም ይሰጠናል? እንዲኽ ከገቢረ ኀጢአት ሳይወጡ አዲስ ዓመትን ማክበር ማለት ለእኔ እንደ ልጆች የዕቃ ዕቃ ጨዋታ ነው፡፡

Saturday, August 30, 2014

አዲሱ ዓመት - ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዳስተማረው (ክፍል ፩)



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ነሐሴ ፳፬ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
 የምወዳችኁ ልጆቼ! አዲሱ ዓመት የደስታ የሰላምና የጤና እንዲኾንላችኁ ትሻላችሁን? እንኪያስ ገና ከዥመሩ በስካር፣ በዘፈን፣ በገቢረ ኀጢአት ለማሳለፍ አታቅዱ፡፡ የአዲሱ ዓመት የመዠመሪያውን ዕለት ብቻ ሳይኾን እያንዳንዱን ቀን በገቢረ ኀጢአት አትዠምሩት፡፡ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ሥራ፣ ምግባር ትሩፋት በመሥራት አሐዱ በሉ እንጂ፡፡ ዕለታት ክፉዎች ወይም ጥሩዎች የሚኾኑት በተፈጥሮአቸው እንደዚያ ኾነው አይደለም፡፡ ዕለቱን ክፉ ወይም ደግ እንዲኾን የምናደርገው እኛው ነን፡፡ የአምናው ማግሰኞ ከዘንድሮ ማግሰኞ የተለየ አይደለም፡፡ የተለየ የሚያደርገው የእኛ ብርታት ወይም ስንፍና ብቻ ነው፡፡

Tuesday, August 12, 2014

ማርያም ፊደል

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ነሐሴ ፯ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
 እንኳን ለዓለም ኹሉ ደስታን ወዳመጣችው ዕለት አደረሳችኁ፤ አደረሰን፡፡ ነሐሴ ሰባት ቀን የባሕርያችን መመኪያ የምትኾን ንጽሕተ ንጹሐን፥ ቅድስተ ቅዱሳን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተፀነሰችበት ዕለት ነው፡፡ ይኽቺን ዕለት ያልናፈቀ ትውልድ የለም፡፡ ጽድቃቸው እንደ መርገም ጨርቅ ለኾነባቸው ቅዱሳን አበው ወእማት ተስፋቸው የሚፈጸመው በዛሬው ዕለት በተጸነሰችው በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ነውና፡፡ ቅድስትና ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያናችንም ከእግዚአብሔር ቀጥሎ እንደ እመቤታችን ከፍ ከፍ የምታደርገው ፍጥረት የሌለው ስለዚኹ ነው፡፡ ሊቃውንቱ፡- “ሐና አንቺን የጸነሰችበት የደስታ ቀን ምን ያኽል የተባረከች የተቀደሰች ቀን ናት፤ ሟች ኢያቄምም ለሕይወት አንቺን  ያፈራባት ቀን ምን ያኽል የተባረከች የተቀደሰች ቀን ናት፤” ብለው የሚዘምሩላትም ይኽን ምሥጢር በልቡናቸው ቋጥረው ነው /አባ ጽጌ ድንግል፤ ማኅሌተ ጽጌ ቁ.፵፬/፡፡

Monday, August 4, 2014

መቅረዝ ዘተዋሕዶ - የውዳሴ ማብራርያ መጽሐፍ በገበያ ላይ ዋለች



መቅረዝ ዘተዋሕዶ ከዚኽ በፊት ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ባዘጋጁት የትርጓሜ መጽሐፍ ተተንተርሳ የተዘጋጀች መጽሐፍ ስትኾን የምትለየውም፡-
፩ኛ) የጥንቱን ለዛ ሳትለቅ ቀለል ባለ አቀራረብና ይዘት በእያንዳንዱ ምዕመን እጅ እንድትደርስ በማሰብመዘጋጀቷ፤
፪ኛ) “እንዲል፣ እንዳለ፣ እንዲሉየሚለውን ጥንታዊ አቀማመጥ ጸሐፊውንና ደራሲውንመለየቷ፤
፫ኛ) አንዳንድ ተጨማሪ ማብራርያ የሚያስፈልጋቸውን ምንባባት ከተለያዩ ድርሳናት ተጨማሪ ማብራሪያመያዟ፤
፬ኛ) የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ በሚያስፈልጋቸው ቦታዎች ላይ ጥቅሱን በማስቀመጥ ምዕመናን እንዲያመሳክሩት መንገድመክፈቷ ነው፡፡

Sunday, August 3, 2014

ፍልሰታ


(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐምሌ ፳፯ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ተዋዳጆች ሆይ!  ዛሬ የምንማማረው በእንተ ፍልሰታ ለማርያም አይደለም፡፡ ስለ ራሳችን ፍልሰታ እንጂ፡፡ ኹላችንም ስለ እመቤታችን ፍልሰታ የመናገር ችግር የለብንም፡፡ ዛሬ እንድንማማርና እንድንወቃቀስ የፈለግኹት በሕይወታችን ከግብርናተ ዲያብሎስ ወደ ክርስቶስ ሳንፈልስ (ሳንሻገር) የእመቤታችንን ፍልሰታ ብቻ ለምናከብር ለየኔ ቢጤዎች ነው፡፡

Friday, July 25, 2014

††† መቅረዝ ዘተዋሕዶ - የውዳሴ ማብራርያ መጽሐፍ በቅርብ ቀን በገበያ ላይ ትውላለች †††


መቅረዝ ዘተዋሕዶ ከዚኽ በፊት ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ባዘጋጁት የትርጓሜ መጽሐፍ ተተንተርሳ የተዘጋጀች መጽሐፍ ስትኾን የምትለየውም በሚከተሉት ዋና ዋና ነጥቦች ነው፡-
፩ኛ) የጥንቱን ለዛ ሳይለቅ ቀለል ባለ አቀራረብና ይዘት በእያንዳንዱ ምዕመን እጅ እንዲደርስ በማሰብ መዘጋጀቷ፤
፪ኛ) “እንዲል፣ እንዳለ፣ እንዲሉ” የሚለውን ጥንታዊ አቀማመጥ ጸሐፊውንና ደራሲውን መለየቷ፤
፫ኛ) አንዳንድ ተጨማሪ ማብራሪያ የሚያስፈልጋቸውን ምንባባት ከተለያዩ ድርሳናት ተጨማሪ ማብራሪያ መያዟ፤
፬ኛ) የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ በሚያስፈልጋቸው ቦታዎች ላይ ጥቅሱን በማስቀመጥ ምዕመናን እንዲያመሳክሩት መንገድ መክፈቷ፡

Friday, July 11, 2014

ብርሃናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐምሌ ፭ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
 በዛሬው ዕለት የምናከብረው በዓል ኹለቱም ታላላቅ ሐዋርያት በሰማዕትነት ያረፉበትን በዓል ነው፡፡ ይኽ ዕለት በየዓመቱ አይለዋወጥም፡፡ የሐዋርያትን ጦም ከጨረስን በኋላ የምናከብረው ነው፡፡ በዚኽ ዕለት ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በቅዳሴዋም በትምህርቷም ኹሉ እነዚኽን ታላላቅ ሐዋርያት ታነሣለች፤ ታወድሳለች፤ ሰማዕትነታቸውንም ለልጆቿ ታስተምራለች፡፡ ምንም እንኳን በእነዚኽ ሐዋርያት ስም የተሰየመ ቤተ ክርስቲያን በብዛት ባይገኝም በአዲስ አበባ ግን “ብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ” የሚባል ቤተ ክርስቲያን አለ፡፡
 ወደ ሰሜኑ የአገራችን ክፍል ስንሔድ ይኽ ዕለት “ሓወርያ” ተብሎ ይጠራል፡፡ ስያሜውም የእነዚኽን ሐዋርያት ሰማዕትነት ለመግለጥና ለማሰብ የተሠጠ ነው፡፡ እረኞች ጅራፋቸውን ገምደው በቡድን በቡድን እየኾኑ ያስጨኹታል፡፡ የጅራፉ ጩኸት የእነዚኽ ሰማዕታት መገረፍ፣ መቁሰል፣ መሰየፍ፣ መሰቃየት፣ መሰቀል የሚያስታውስ ነው፡፡ አባቶቻችን ክርስትናውን ማንበብና መጻፍ ወደማይችለው ማኅበረ ሰብእ ምን ያኽል እንዳሰረጹትም ከዚኽ እንገነዘባለን፡፡ እኛ ግን እንኳንስ ለተማረው ማስተማር ይቅርና አባቶቻችን የሠሩትን እንኳን መጠበቅ አቅቶናል፡፡

Wednesday, July 9, 2014

ለመቅረዝ ዘተዋሕዶ ድረ ገጽ ወዳጆች

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐምሌ ፪ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!



መቅረዝ ዘተዋሕዶ መንፈሳዊት ድረ ገጽ አድራሻ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህሕዶን እምነት ሥርዓት ትውፊትና ታሪክ መሠረት ያደረጉ ትምህርታዊ የኾኑ ጽሑፎች በአራት በተለያዩ ቋንቋዎች ላለፉት ዓመታት ወጥተዋል፡፡ እነዚኽ ትምህርቶች በሀገር ውስጥም ኾነ ከሀገር ውጪ የኢንተርኔት አቅርቦት ላላቸው ምዕመናን በተቻለ መጠን ለማድረስ ተሞክሯል፡፡ ነገር ግን እነዚኽን መንፈሳውያን ጽሑፎች በዓቅም ማነስ ምክንያት ቴክኖሎጂውን መጠቀም ላልቻሉ  ምዕመናን ሊዳረሱ አልቻሉም፡፡

Friday, June 20, 2014

“መልካሙን የእምነት ገድል ተጋደል” 1 ጢሞ. 6፣16



በቀሲስ ጥላሁን ታደሰ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሰኔ 13 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለመንፈስ ልጁ ጢሞቴዎስ በላከለት የመጀመሪያው መልእክት ማጠቃለያ ላይ የምናገኘው ኃይለ ቃል ነው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስይህንን መልእክት ከአቴና በደቀ መዝሙሩ በቲቶ በኩል ልኮለታል፡፡ ይሄንን የመጀመሪያ መልእክት ቅዱስ ጳውሎስ ወደ መቄዶንያ በሔደጊዜ፤ ደቀ መዝሙሩ ጢሞቴዎስን በሃገረ ኤፌሶን ትቶት ሔዶ ነበር፡፡ በዚያ ቆይታው ስለ መንፈሳዊ አገልግሎቱና /እርሱም/ በመንፈሳዊሕይወቱ ሊፈጽማቸው ስለሚገቡ ጉዳዮች ሊያስረዳው ጽፎለታል፡፡

Monday, June 9, 2014

ጾምን ቀድሱ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሰኔ ፪ ቀን፥ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡-  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
 የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ. ምእመን ኾኖ ስለ ጾም ምንነትና አስፈላጊነት የማያውቅ አለ ማለት አይቻልም፡፡ ከ፯ ዓመታችን አንሥተን አብዛኞቻችን ከጾም ጋር ተዋውቀናልና፡፡ ጾም የሥጋን ምኞት እንደምታጠፋ፣ የነፍስን ቁስል እንደምትፈውስ፣ ጽሙናንና ርጋታን እንደምታስተምር፣ ከእንስሳዊ ግብር እንደምትጠብቅ፣ ሰውን መልአክ ዘበምድር አድርጋ መንፈሳዊ ኃይልን እንደምታስታጥቅ አብዛኞቻችን ተምረነዋል፤ በቃላችንም እናውቀዋለን፡፡ ነገር ግን በተግባር እግዚአብሔር እንደወደደው የሚጾሙት እጅግ ጥቂቶች መኾናቸው በጣም አሳዛኝ ነው፡፡ ብዙዎቻችን የሥጋ ፈቃዳችንን ሳንተው “ስለምንጾም” በሕይወታችን ለውጥ አይታይብንም፡፡

Saturday, June 7, 2014

በዓለ ጰራቅሊጦስ



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፥ ግንቦት ፴ ቀን፥ ፳፻፮ ዓ.ም)፡ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
  “ጰራቅሊጦስ” ማለት በጽርዕ ልሳን “አጽናኝ” ማለት ነው፡፡ ምንም እንኳን በ፩ኛ ዮሐ.፪፡፩ ላይ ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ተጠቅሶ ብናገኘውም፥ አብዛኛውን ጊዜ ግን ከሦስቱ አካላተ ሥላሴ አንዱ ለሚኾን ለመንፈስ ቅዱስ የሚሰጥ ስያሜ ነው /ዮሐ.፲፬፡፲፮/፡፡ ይኸውም የመንፈስ ቅዱስን ግብር የሚገልጥ ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስ በበዓለ ኃምሳ ቤተ ክርስቲያንን በአሚነ ሥላሴ አጽንቶ ዓለምንም ኹሉ ወደ እውነት እንዲመራት መውረዱን የሚያመለክት ነው፡፡

FeedBurner FeedCount