Monday, November 10, 2014

ለይሖዋ ምስክሮች ኑፋቄ የተሰጠ ምላሽ (ክፍል ሦስት)

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ማግሰኞ ኅዳር 2 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
የሥላሴ ትምህርት በቅድመ ኒቅያ አበው
ውድ የመቅረዝ ተከታታዮች እንደምን ሰነበታችኁ? በጥያቄና መልስ ዓምዳችን ለይሖዋ ምስክሮች የስሕተት ትምህርት ኦርቶዶክሳዊ ምላሽ መስጠት ከዠመርን የዛሬው ሦስተኛው ክፍል ነው፡፡ በክፍል አንድ ምላሻችን የይሖዋ ምስክሮች የስሕተት ትምህርቶች ምን ምን እንደኾኑ፥ እንዲኹም መሠረታዊ የምሥጢረ ሥላሴን ትምህርት በመጠኑ ዐይተናል፡፡ በክፍል ኹለት ትምህርታችንም ከብሉይ እና ከሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት በማመሳከር ምሥጢረ ሥላሴ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርት እንደኾነ ተመልክተናል፡፡ ለዛሬ ደግሞ እግዚአብሔር በረዳን መጠን ከሐዋርያነ አበው ዠምረን እስከ ሦስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበሩ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ምን ብለው እንዳስተማሩ እንመለከታለን፡፡ ይኽን የምናደርግበት ምክንያትም የይሖዋ ምስክሮች የሥላሴ ትምህርት የተወሰነው በ325 ዓ.ም. በጉባኤ ኒቅያ በንጉሥ ቈስጠንጢኖስ አስገዳጅነት ነው ስለሚሉ ነው፡፡ እግዚአብሔር ዓይነ ልቡናችንን ያብራልን አሜን!!!

Wednesday, November 5, 2014

አምስቱ ስጦታዎች

በቀሲስ ፋሲል ታደሰ




(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ጥቅምት 27 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!! 

ሥርዓተ አምልኮ ከሚገለጥበት መንገድ አንዱ ስጦታ ነው፡፡ የሰው ልጅ ከራሱ የኾነ አንዳች የለውም፤ በጎ የኾነው ኹሉ ከፈጣሬ ዓለማት ከእግዚአብሔር ያገኘው ነው፡፡ በመኾኑም ፈጣሪያችን መስጠትን እንዳስተማረን ኹሉ እኛም ተገዥነታችንን ከምንገልጥበት አንዱ ከርሱ የተቀበልነውን በፈቃደኝነት በደስታ በመስጠት ነው፡፡ ነቢዩ ዳዊት ይኽን ሲያስረዳ “ኹ ከአንተ ዘንድ ነውና፡ ከእጅህ የተቀበልነውን ሰጥተንሃልና ይኽን ያኽል ልናቀርብልህ የቻልን ማነን? በፈቃዴ ይህን አቅርቤአለሁበማለት ከእግዚአብሔር ያገኘውን ሀብት በደስታ በፈቃዱ ለቤተ መቅደስ ሥራ እንዲውል መስጠቱን በመግለጽ ስለ ስጦታ ጽፏል /1ዜና 29÷9-16/፡፡

Monday, November 3, 2014

ትምህርተ ሃይማኖት (ክፍል አምስት)


(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ጥቅምት 25 ቀን፣ 2007 ..)- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!


ሐ) ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ አረዳድ


 እንደምን ሰንበታችኁ ውድ የመቅረዝ ተከታታዮች? ትምህርተ ሃይማኖት በሚለው ተከታታይ ትምህርታችን ውስጥ ለዛሬ ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ኦርቶዶክሳዊ አረዳድን እንማማራለን፡፡ በዚኽ ጽሑፍ ውስጥ ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ምንነት፤ በቤተ ክርስቲያን ያለው ቦታ ምን እንደሚመስልና እንዴት መረዳት እንዳለብን እና ሌሎች ተያያዥ ሐሳቦችን እንመለከታለን፡፡ መልካም ንባብ፡፡

Wednesday, October 29, 2014

ስለ አቤልና ቃየን (ለሕፃናት)

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ጥቅምት 20፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
የተዋሕዶ ፍሬዎች፣ የሃገር ተስፋዎች እንደምን ሰነበታችኁ ልጆች? “እግዚአብሔር ይመስገን ደኅና ነን” አላችችኁ? መልካም፡፡ ትምህርት እንዴት ነው? እየጐበዛችኁ ነው አይደል? ጠንከር ብላችኁ በማጥናት ከአምናው የተሻለ ውጤት ለማምጣት እንደተዘጋጃችኁ ተስፋ አደርጋለኹ፤ በርቱ እሺ?
  ዛሬ አቤል እና ቃየን ስለሚባሉ ኹለት ወንድማማቾች ታሪክ ነው ይዤላችኁ የመጣኹት፡፡ ለመስማት ዝግጁ ናችኁ አይደል? በጣም ጥሩ!!!
 አዳምና ሔዋን በገነት ይኖሩ ነበር፡፡ ሲበድሉ ግን እግዚአብሔር ከገነት አስወጣቸው፡፡ ደብር ቅዱስ ወደ ተባለ ቦታም ተሰደዱ፡፡ ከዚኽ ቦታ ኾነውም የገነት ሽታ እየሸተታቸው ይኖሩ ነበር፡፡ ወደ ገነት ግን መቅረብ አልተቻላቸውም፡፡ ሦስት ዓመት ሙሉም በጣም ያለቅሱና ያዝኑ ነበር፡፡

Monday, October 27, 2014

ወደ እግዚአብሔር ለመድረስ (መንደርደሪያ)



በዲ/ን ሳምሶን ወርቁ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ጥቅምት 17 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
በክርስትና ሕይወት ውስጥ ምዕመናን ስለመንፈሳዊነት ያላቸው ግንዛቤ ብዙ ጊዜ ያልተሟላ አንዳንዴ የተሳሳተ ብቻ ሳይሆን መንፈሳዊነት ብለው የሚያስቡት መንፈሳዊነት ያልሆነውን ሆኖ ይገኛል፡፡ ከዚህ የተነሣ ብዙዎች መንፈሳዊያን ናቸው ብለው የሚያስቧቸውን ሰዎች ሕይወት ተመልክተው መንፈሳዊነት እንዲህ ከሆነ ይቅርብኝ እስከማለት ይደርሳሉ፡፡ ነገር ግን መንፈሳዊነት ትርጉሙ ዓላማው ምስጢሩ የረቀቀ የጠለቀ ነው፡፡

Saturday, October 25, 2014

እኔ ነኝ፥ አትፍሩ



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ጥቅምት 15 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 ከዕለታት በአንዲቱ ቀን ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ምድር በተመላለሰ ጊዜ ወደ ምኵራብ ገባ፡፡ እንደ ባለ ሥልጣንም ያስተምራቸው ነበር፡፡ ብዙዎች ግን ሰምተው ተገረሙና፡- “እነዚህን ነገሮች ይህ ከወዴት አገኛቸው? ለዚህ የተሰጠችው ጥበብ ምንድር ናት? በእጁም የሚደረጉ እንደነዚህ ያሉ ተአምራት ምንድር ናቸው? ይህስ ጸራቢው የማርያም ልጅ የያቆብም የዮሳም የይሁዳም የስምዖንም ወንድም አይደለምን? እኅቶቹስ በዚህ በእኛ ዘንድ አይደሉምን?” እያሉ ይሰናከሉበት ነበር /ማር.6፡3/

Sunday, October 19, 2014

ትምህርተ ሃይማኖት (ክፍል አራት)




(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ጥቅምት 9 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!



ለ) ቅዱስ ትውፊት (Holy Tradition)


ትርጕም

 በሰዋስዋዊ ዘይቤው ሲፈታ፥ ትወፊት ማለት ስጦታ፣ ልማድ፣ ትምህርት፣ ወግ፣ ታሪክ፣ ሃይማኖት፣ ሥርዓት፣ ከጥንት ከአበው ሲያያዝ ሲወርድ፥ ቃል በቃል ሲነገር የመጣ ማለት ነው /አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፣ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ፣ ገጽ፣ 397/፡፡ ጽርዓውያንም “ፓራዶሲስ” ይሉታል፤ አንድን ነገር እጅ በእጅ ለሌላ ሰው ማስረከብን ወይም ማቀበልንም ያመለክታል፡፡ ዕብራውያን ደግሞ “ማሳር - ማቀበል” እና “ቂብል - መቀበል” የሚሉ ቃላትን ይጠቀማሉ፡፡

Wednesday, October 15, 2014

ለይሖዋ ምስክሮች ኑፋቄ የተሰጠ ምላሽ (ክፍል ኹለት)



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ጥቅምት 5 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

ምስጢረ ሥላሴ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርት ነው!!!

 የምስጢረ ሥላሴ ትምህርት እግዚአብሔር የገለጠው እውነት እንጂ የይሖዋ ምስክሮች እንደሚሉት ሰዋዊ ትምህርት አይደለም፡፡ ቃሉን በቀጥታ ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንፈልገው ብሎ መጠየቅ ግን የዕውቀት ማነስ ነው፡፡ ምክንያቱም የሚፈለገው የትምህርቱ መኖር እንጂ የቃሉ መኖር አይደለምና፡፡ እንኳንስ ሥላሴ የሚለው ቃል ይቅርና መጽሐፍ ቅዱስ የሚል ቃል እንኳን በራሱ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አናገኘውም፡፡

Sunday, October 12, 2014

ስለ አዳምና ሔዋን (ለሕፃናት)



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ጥቅምት 03 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
       
የእግዚአብሔር ልጆች እንደምን ሰነበታችኁ? ደኅና ናችኁ? ትምህርት እንዴት ነው? ጐበዞች፡፡

ባለፈው ጊዜ ስለ ምን እንደተማርን ታስታውሳላችኁ ልጆች? ጐበዞች፡፡ የተማማርነው ስለ ሥነ ፍጥረት ነው አይደል? እስኪ ካስታወሳችኁ አዳምና ሔዋን መቼ ተፈጠሩ ነበር ያልነው? ጐበዞች፡፡ ልክ ናችኁ፡፡ ዓርብ ነበር የተፈጠሩት፡፡ ዛሬ ደግሞ ስለ አዳምና ስለ ሔዋን ታሪክ እነግራችኋለኁ፡፡ እናንተም ለመስማት ዝግጁ ናችኁ አይደል? ጐበዞች፡፡ 

Friday, October 10, 2014

ማኅሌተ ጽጌ፤ ምንጩ ትርጉሙና መልእክቱ (የመጨረሻው ክፍል)



በዲ/ ያረጋል አበጋዝ

 
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መስከረም 30 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡


የቀጠለ…

4.4.
ማዕረረ ትንቢት ማርያም ዘመነ ጽጌ እንግዳ  
ወዘመነ ፍሬ ጽጋብ ዘዓመተ ረኃብ ፍዳ
ብኪ ተአምረ ዘይቤ ኢዩኤል ነቢየ ኤልዳ
ያንጸፈጽፍ እምአድባሪሁ ወእም አውግሪሁ ለይሁዳ
ፀቃውዓ መዓር ጥዑም ወሃሊብ ፀዓዳ»
ትርጉም
«
በመከር ጊዜ አበባ በአበባ ጊዜ ደግሞ መከር አዝመራ ማጨድና መሰብሰብ የለም፡፡ ምክንያቱም ጊዜያቸው የተለያየ ስለሆነ፡፡ ለምሳሌ በመስከረም ወር የአበባ ጊዜ በመሆኑ አዝመራ መሰብሰብ የለም፡፡»

Wednesday, October 8, 2014

ማኅሌተ ጽጌ፤ ምንጩ ትርጉሙና መልእክቱ (ክፍል ሦስት)



በዲ/ ያረጋል አበጋዝ

 
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መስከረም 28 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡


የቀጠለ…


4. ምሥጢር
በዚህ ርዕሰ ጉዳይ የምናየው በብሉይና በሐዲስ የተነገረውን እያመሰጠረ፣ በብዙ አምሳልና ትንቢት ይነገር የነበረውን የአምላክን ከድንግል መወለድ፣ ትንቢቱን ከፍጻሜው ጋር እያዛመደ የሚናገረውን ነው፡፡ ከዚህም ውስጥ የተወሰኑትን እናያለን፡፡

Monday, October 6, 2014

ማኅሌተ ጽጌ፤ ምንጩ ትርጉሙና መልእክቱ (ክፍል ሁለት)



በዲ/ ያረጋል አበጋዝ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መስከረም 26 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡


የቀጠለ…


2. ታሪክ

በብሉይና በሐዲስ ኪዳን በተለያዩ ጊዜያት የተፈጸሙትን ድርጊቶች እያነሣ የሚሔድና በዚያውም ከታሪኩ ጋር አብሮ ጸሎትና ምሥጢር የያዘ ነው፡፡ ታሪክን ከሚያነሡት መካከል የሚከተሉትን ለአብነት መመልከት ይቻላል፡፡

FeedBurner FeedCount