Showing posts with label ስብከት ወተግሳጽ. Show all posts
Showing posts with label ስብከት ወተግሳጽ. Show all posts

Wednesday, December 31, 2014

“ነገር ኹሉ ለበጐ እንዲደረግ እናውቃለን” /ሮሜ.8፡28/

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐሙስ ታኅሳስ 23 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
  አንዳንዴ በሕይወታችን ምንም የማይጠቅሙ ነገሮችን ልንመርጥ እንችላለን፡፡ የሚያስፈልገንና የሚጠቅመን ግን መንፈስ ቅዱስ ሲመርጥልን ነው፡፡ አደጋና ስጋት፣ በሽታና ስቃይ፣ እጦትና ችግር፣ ራብና ጥማት፣ ኀዘንና ትካዜ የሌለው ሕይወት እጅግ ጠቃሚ እንደኾነ አድርገን እናስባለን፡፡ ነገር ግን ይኽ የሌለው ሕይወት ኹሉ ጠቃሚም ላይኾን ይችላል፡፡
  እስኪ የሐዋርያው የቅዱስ ጳውሎስን ሕይወት እንደ ምሳሌ አንሥተን እንመልከተው፡፡ እግዚአብሔር በሰጠው ሀብተ ፈውስ የዕውራንን ዐይን የሚያበራው፣ የለምጻሞችን ለምጽ የሚያነጻው፣ ሙታንን የሚያነሣው፣ ሌላ ይኽን የመሰለ ተአምራትን የሚያደርግ ታላቁ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ሥጋውን የሚጐስም የሰይጣን መልእክተኛ ነበረው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ የሰይጣን መልእክተኛ ያለው አባቶች በሦስት መንገድ ይተረጕሙታል፡፡ ሰይጣን ማለት ጠላት፣ ክፉ፣ ተቃዋሚ ማለት ነውና /1ኛ ነገ.5፡4/ ቅዱስ ጳውሎስ የሰይጣን መልእክተኛ ተሰጠኝ ሲል፡-

Saturday, October 25, 2014

እኔ ነኝ፥ አትፍሩ



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ጥቅምት 15 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

 ከዕለታት በአንዲቱ ቀን ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ምድር በተመላለሰ ጊዜ ወደ ምኵራብ ገባ፡፡ እንደ ባለ ሥልጣንም ያስተምራቸው ነበር፡፡ ብዙዎች ግን ሰምተው ተገረሙና፡- “እነዚህን ነገሮች ይህ ከወዴት አገኛቸው? ለዚህ የተሰጠችው ጥበብ ምንድር ናት? በእጁም የሚደረጉ እንደነዚህ ያሉ ተአምራት ምንድር ናቸው? ይህስ ጸራቢው የማርያም ልጅ የያቆብም የዮሳም የይሁዳም የስምዖንም ወንድም አይደለምን? እኅቶቹስ በዚህ በእኛ ዘንድ አይደሉምን?” እያሉ ይሰናከሉበት ነበር /ማር.6፡3/

Sunday, September 7, 2014

አዲሱ ዓመት - ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዳስተማረው (የመጨረሻው ክፍል - ክፍል ፬)



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ጳጉሜ ፪ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
የቀጠለ…
 እግዚአብሔር የሚወዳችኁ እናንተም የሚምትወዱት ልጆቼ! ይኽን ኹሉ በዝርዝር የምነግራችኁ ለምን ይመስላችኋል? ይኽን ኹሉ በዝርዝር መናገሬ በዘዴ ኹላችንም የምናደርገውን ማናቸውም እንቅስቃሴያችን ለእግዚአብሔር ክብር እናደርገው ዘንድ ስለምሻ ነው፡፡ በባሕር የሚነግዱ ነጋዴዎች ንብረታቸውን ወደ ከተማ ዳር መልሕቅ ካመጡ በኋላ መዠመሪያ የሚያደርጉት ነገር ቢኖር በቀጥታ ወደ ገበያ ሥፍራ መሔድ አይደለም፡፡ ወደ ገበያ ሥፍራ ከመሔዳቸው በፊት ስለ ትርፋቸው ያስባሉ እንጂ፡፡ እኛም በምናደርገው ኹሉ ከእግዚአብሔር ዘንድ የምናገኘውን ጥቅም ማሰብ አለብን፡፡

Saturday, September 6, 2014

አዲሱ ዓመት - ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዳስተማረው (ክፍል ፫)



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ጳጉሜ ፩ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
የቀጠለ…                       
 ለእግዚአብሔር ክብር ብሎ ሰውን መውቀስም አለ፡፡ ከእናንተ መካከል፡- “እንዴት ብሎ? ርግጥ ነው ብዙውን ጊዜ ሠራተኞቻችንን እንወቅሳለን፡፡ ለእግዚአብሔር ክብር ብሎ መውቀስስ እንደምን ያለ ነው?” አዎ! የሚሰክር ወይም የሚሰርቅ ሠራተኛ ወይም ጓደኛ ብናይ ወይም ከዘመዳችን አንዱ ወደ ተውኔት ቤት፣ ወይም ለነፍሱ ምንም ረብሕ ወደማያገኝበት ሥፍራ ሲሮጥ፣ በከንቱ ሲምል፣ የሐሰት ምስክርነትን ሲሰጥ፣ ወይም ሲዋሽ፣ ወይም ሲቈጣ ብናየው ዠርባችንን ብንሰጠውና ብንገሥፀው ወቀሳችን ለእግዚአብሔር ክብር የተደረገ ነው ይባላል፡፡

Tuesday, September 2, 2014

አዲሱ ዓመት - ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዳስተማረው (ክፍል ፪)




(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ነሐሴ ፳፯ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
የቀጠለ…

 ከገቢረ ኀጢአት ሳይወጡ አዲስ ዓመት ሲመጣ መደሰት፣ ብዙ መብልና መጠጥ ማዘጋጀት፣ አዲስ ልብስም መልበስ ጥቅም የለውም፡፡ ነፍሳችን በኀጢአት እየተጨነቀች፣ ነፍሳችን ተርባና ተጠምታ ሳለ፣ የተዳደፈ የኀጢአት ልብስም ተጆቡና ሳለ አዲስ ዓመት ማክበር ለእኛ ምን ጥቅም ይሰጠናል? እንዲኽ ከገቢረ ኀጢአት ሳይወጡ አዲስ ዓመትን ማክበር ማለት ለእኔ እንደ ልጆች የዕቃ ዕቃ ጨዋታ ነው፡፡

Saturday, August 30, 2014

አዲሱ ዓመት - ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዳስተማረው (ክፍል ፩)



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ነሐሴ ፳፬ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
 የምወዳችኁ ልጆቼ! አዲሱ ዓመት የደስታ የሰላምና የጤና እንዲኾንላችኁ ትሻላችሁን? እንኪያስ ገና ከዥመሩ በስካር፣ በዘፈን፣ በገቢረ ኀጢአት ለማሳለፍ አታቅዱ፡፡ የአዲሱ ዓመት የመዠመሪያውን ዕለት ብቻ ሳይኾን እያንዳንዱን ቀን በገቢረ ኀጢአት አትዠምሩት፡፡ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ሥራ፣ ምግባር ትሩፋት በመሥራት አሐዱ በሉ እንጂ፡፡ ዕለታት ክፉዎች ወይም ጥሩዎች የሚኾኑት በተፈጥሮአቸው እንደዚያ ኾነው አይደለም፡፡ ዕለቱን ክፉ ወይም ደግ እንዲኾን የምናደርገው እኛው ነን፡፡ የአምናው ማግሰኞ ከዘንድሮ ማግሰኞ የተለየ አይደለም፡፡ የተለየ የሚያደርገው የእኛ ብርታት ወይም ስንፍና ብቻ ነው፡፡

Tuesday, August 12, 2014

ማርያም ፊደል

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ነሐሴ ፯ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
 እንኳን ለዓለም ኹሉ ደስታን ወዳመጣችው ዕለት አደረሳችኁ፤ አደረሰን፡፡ ነሐሴ ሰባት ቀን የባሕርያችን መመኪያ የምትኾን ንጽሕተ ንጹሐን፥ ቅድስተ ቅዱሳን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተፀነሰችበት ዕለት ነው፡፡ ይኽቺን ዕለት ያልናፈቀ ትውልድ የለም፡፡ ጽድቃቸው እንደ መርገም ጨርቅ ለኾነባቸው ቅዱሳን አበው ወእማት ተስፋቸው የሚፈጸመው በዛሬው ዕለት በተጸነሰችው በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ነውና፡፡ ቅድስትና ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያናችንም ከእግዚአብሔር ቀጥሎ እንደ እመቤታችን ከፍ ከፍ የምታደርገው ፍጥረት የሌለው ስለዚኹ ነው፡፡ ሊቃውንቱ፡- “ሐና አንቺን የጸነሰችበት የደስታ ቀን ምን ያኽል የተባረከች የተቀደሰች ቀን ናት፤ ሟች ኢያቄምም ለሕይወት አንቺን  ያፈራባት ቀን ምን ያኽል የተባረከች የተቀደሰች ቀን ናት፤” ብለው የሚዘምሩላትም ይኽን ምሥጢር በልቡናቸው ቋጥረው ነው /አባ ጽጌ ድንግል፤ ማኅሌተ ጽጌ ቁ.፵፬/፡፡

Friday, June 20, 2014

“መልካሙን የእምነት ገድል ተጋደል” 1 ጢሞ. 6፣16



በቀሲስ ጥላሁን ታደሰ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሰኔ 13 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለመንፈስ ልጁ ጢሞቴዎስ በላከለት የመጀመሪያው መልእክት ማጠቃለያ ላይ የምናገኘው ኃይለ ቃል ነው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስይህንን መልእክት ከአቴና በደቀ መዝሙሩ በቲቶ በኩል ልኮለታል፡፡ ይሄንን የመጀመሪያ መልእክት ቅዱስ ጳውሎስ ወደ መቄዶንያ በሔደጊዜ፤ ደቀ መዝሙሩ ጢሞቴዎስን በሃገረ ኤፌሶን ትቶት ሔዶ ነበር፡፡ በዚያ ቆይታው ስለ መንፈሳዊ አገልግሎቱና /እርሱም/ በመንፈሳዊሕይወቱ ሊፈጽማቸው ስለሚገቡ ጉዳዮች ሊያስረዳው ጽፎለታል፡፡

Monday, June 9, 2014

ጾምን ቀድሱ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሰኔ ፪ ቀን፥ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡-  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
 የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ. ምእመን ኾኖ ስለ ጾም ምንነትና አስፈላጊነት የማያውቅ አለ ማለት አይቻልም፡፡ ከ፯ ዓመታችን አንሥተን አብዛኞቻችን ከጾም ጋር ተዋውቀናልና፡፡ ጾም የሥጋን ምኞት እንደምታጠፋ፣ የነፍስን ቁስል እንደምትፈውስ፣ ጽሙናንና ርጋታን እንደምታስተምር፣ ከእንስሳዊ ግብር እንደምትጠብቅ፣ ሰውን መልአክ ዘበምድር አድርጋ መንፈሳዊ ኃይልን እንደምታስታጥቅ አብዛኞቻችን ተምረነዋል፤ በቃላችንም እናውቀዋለን፡፡ ነገር ግን በተግባር እግዚአብሔር እንደወደደው የሚጾሙት እጅግ ጥቂቶች መኾናቸው በጣም አሳዛኝ ነው፡፡ ብዙዎቻችን የሥጋ ፈቃዳችንን ሳንተው “ስለምንጾም” በሕይወታችን ለውጥ አይታይብንም፡፡

Saturday, June 7, 2014

በዓለ ጰራቅሊጦስ



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፥ ግንቦት ፴ ቀን፥ ፳፻፮ ዓ.ም)፡ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
  “ጰራቅሊጦስ” ማለት በጽርዕ ልሳን “አጽናኝ” ማለት ነው፡፡ ምንም እንኳን በ፩ኛ ዮሐ.፪፡፩ ላይ ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ተጠቅሶ ብናገኘውም፥ አብዛኛውን ጊዜ ግን ከሦስቱ አካላተ ሥላሴ አንዱ ለሚኾን ለመንፈስ ቅዱስ የሚሰጥ ስያሜ ነው /ዮሐ.፲፬፡፲፮/፡፡ ይኸውም የመንፈስ ቅዱስን ግብር የሚገልጥ ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስ በበዓለ ኃምሳ ቤተ ክርስቲያንን በአሚነ ሥላሴ አጽንቶ ዓለምንም ኹሉ ወደ እውነት እንዲመራት መውረዱን የሚያመለክት ነው፡፡

Wednesday, May 28, 2014

ዕርገተ ክርስቶስ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ግንቦት ፳ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ከተነሣ በኋላ ዕለቱን ወደ ሰማይ አላረገም፡፡ ወንጌላዊው ሉቃስ እንደሚነግረን ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያረገው ከሙታን ተለይቶ ከተነሣ በኋላ በ፵ኛው ቀኑ ላይ ነው፡፡ በእነዚኽ ፵ ቀናት ውስጥም ብዙውን ጊዜ ለደቀ መዛሙርቱ እየተገለጠ ብዙ ምሥጢርና ሥርዓተ ሐዲስ አስተምሯቸዋል፡፡ የተማሩትን ኹሉ እንዲጠብቁ፣ ዓለምን ኹሉ በወንጌል መረብ እንዲያጠምዱ ትእዛዝ ሰጥቷቸዋል፡፡

Wednesday, May 14, 2014

መንፈሳዊ ሕይወት ከትንሣኤ እስከ ጰራቅሊጦስ - የመጨረሻው ክፍል



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ግንቦት ፮ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
5. እስክንገለጥ ድረስ ተሰውረናል

  ከማይበሉ የዓሣ ዝርያ ውስጥ የሚመደብ “ኦይስተር” የተባለ ዓሣ አለ፡፡ በሰውነቱ ውስጥም ለጌጣ ጌጥ የሚያገለግል ቅርፊት አለው፡፡ ነገር ግን ይኽ ዓሣ እስካልተገለጠ ድረስ ይኽ ክብሩ አይታይም፡፡ የእኛም እንደዚኹ ነው፡፡ ክርስቶስ እስካልተገለጠ ድረስ ክብራችን አይገለጥም፤ የተሰወረ ነው፡፡ ሕይወታችን ገና ያልተገለጠና የተሰወረ ከኾነ በዚኽ ዓለም መኖር ያለብን እንደሞተ ሰው ነው፡፡ ለምን? ሕይወታችን ክርስቶስ በክብር ሲገለጥ እኛም በክብር እንገለጥ ዘንድ፡፡

Monday, May 12, 2014

መንፈሳዊ ሕይወት ከትንሣኤ እስከ ጰራቅሊጦስ - ክፍል ፭



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ግንቦት ፬ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

4. እንገለጣለን፡፡
  እስከ ፍጻሜ ድረስ በዚኽ በተቀመጥንበት ስፍራችን የምንቈይ ከኾነ ክርስቶስ በክብር በሚገለጥበት ወራት በክብር እንገለጣለን፡፡ ከተቀመጥንበት ሰማያዊ ስፍራችን ለቅቀን የምንነሣ ከኾነ ግን የምንገለጠው ከክርስቶስ ጋር በክብር አይደለም፤ የዲብሎስን መልክ ይዘን በሐሳር ነው እንጂ፡፡ ስለዚኽ አኹን ከዚያ ስፍራ ለቅቆ መኖር የእኛ መገለጫ አይደለም፡፡ ይኽ ሕይወት ሌላ፣ ያም ሕይወት ሌላ ነውና፡፡ ክርስቶስ አኹን አልተገለጠም፡፡ የእኛም ሕይወት ገና አልተገለጠም፡፡ ስለዚኽ በክብር እስክንገለጥ ድረስ እዚያ ልንቈይ ያስፈልጋል፡፡ መቼ ነው ታድያ የምንገለጠው? ሕይወታችን ክርስቶስ በክብር ሲገለጥ፤ ዳግም ሲመጣ፡፡ እርሱ ሲገለጥ ሕይወታችን ይገለጣል፤ ክብራችን ይገለጣል፤ ደስታችን ይገለጣል፡፡

Monday, May 5, 2014

መንፈሳዊ ሕይወት ከትንሣኤ እስከ ጰራቅሊጦስ - ክፍል ፬



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ ፳፯ ቀን፣ ፳፻፮ ..)- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!


3. ተቀምጠናል

 ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አኹን በክበበ ትስብእት ያለው በምድር ሳይኾን በሰማያዊው ስፍራ ነው፡፡ ክርስቶስ ያለው በባሕርይ አባቱ ዕሪና ተቀምጦ ነው፡፡ እኛም፡- “ወአንሥአነ ወአንበረነ ምስሌሁ በሰማያት በኢየሱስ ክርስቶስ - ከእርሱ ጋር አስነሣን፤ በክርስቶስ ኢየሱስም በሰማያዊ ስፍራ ከእርሱ ጋር አስቀመጠን” እንዲል ከእርሱ ጋር ተዋሕደን ስለተነሣን ያለነው በሰማያዊ ስፍራ ነው ማለት ነው /ኤፌ.፪፡፯/፡፡ ክርስቶስ ኢየሱስ ተቀመጠ መባሉ የእኛን መቀመጥ መናገሩ ነው፤ ዳግም ከውኃና ከመንፈስ ስንወለድ የእርሱ ሕዋሳት ኾነናልና፡፡ ስለዚኽ ከክርስቶስ ጋር ተዋሕደን ለመኖር ትንሣኤ ልቡናን ከተነሣን በኋላ ሰማያዊ ግብራችንን ትተን በምድራዊ ግብር ብቻ መያዝ ክርስቲያናዊ ተፈጥሯችን አይደለም፡፡ ክርስቲያናዊ ተፈጥሯችንን ካልለቀቅን በስተቀር ይኽን ማድረግ አንችልም፡፡  

Friday, May 2, 2014

መንፈሳዊ ሕይወት ከትንሣኤ እስከ ጰራቅሊጦስ - ክፍል ፫

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ ፳፭ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
2.    ተነሥተናል
   ሐዋርያው፡- “ሞታችኋልና” ብሎ አላቆመም፤ ጨምሮም፡- “እንግዲኽ ከክርስቶስ ጋር ከተነሣችኁ” በማለት እንደተነሣንም ነገረን እንጂ፡፡ በጥምቀት ውኃ ሞቱን በሚመስል ሞት ስንሞት፥ አሮጌው ሰውነታችን እንደ ግብጻውያን ተቀብሮ ቀርቷል፡፡ አዲሱ ሰውነታችን ግን እስራኤላውያን ባሕሩ ተከፍሎላቸው እንደተሻገሩ ተሻግሯል (ተነሥቷል)፡፡ ብልየት ያለበት የቀዳማዊ አዳም ሰውነታችን በግብረ መንፈስ ቅዱስ ተቀብሮ አዲሱ ሰውነታችን ሕይወትን አግኝቶ ተነሥቷል፡፡ መሬታዊው ሰዋችን ሞቶ ሰማያዊው ሰዋችንን ለብሰን መንፈሳውያን ኾነናል፡፡ ወደ ጥንተ ተፈጥሯችን ተመልሰናል፡፡

Wednesday, April 30, 2014

መንፈሳዊ ሕይወት ከትንሣኤ እስከ ጰራቅሊጦስ - ክፍል ፪



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ ፳፪ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
 ውድ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች! በክፍል ፩ ትምህርታችን ከትንሣኤ እስከ ጰራቅሊጦስ ባለው እሑድ ለምን ሱባኤ እንደማይገባ፣ ሰይጣን ይኽን ዓላማ እንዴት እንድንስተው እንዳደረገን፣ በመጨረሻም ይኽን የዲያብሎስን ደባ እንደምን ከንቱ ማድረግ ይቻለናል የሚል ጥያቄ አንሥተን ነበር ያቆምነው፡፡ እስኪ ካቆምንበት እንቀጥልና ለዚኽ ይረዳን ዘንድ አንድ ኃይለ ቃልን መነሻ በማድረግ ለመማማር እንሞክር፡፡ እግዚአብሔር ዓይነ ልቡናችንን ያብራልን፡፡ አሜን!!!

Monday, April 28, 2014

መንፈሳዊ ሕይወት ከትንሣኤ እስከ ጰራቅሊጦስ - ክፍል ፩

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ ፲፱ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
  የዚኽ ትምህርት መሠረታዊ ዓላማ ክርስቲያኖች ከትንሣኤ እስከ ጰራቅሊጦስ ባለው ወራት ውስጥ መንፈሳዊ ሕይወታቸው እንዳይቀዘቅዝ ማበረታታት ነው፡፡
  በቤተ ክርስቲያናችን ሥርዓት መሠረት ከትንሣኤ እስከ ጰራቅሊጦስ እሑድ ባለው ወራት ረቡዕንና ዓርብን ጨምሮ አይጦምም፤ አይሰገድምም፡፡ ይኽም ሠለስቱ ምዕት በ፫፻፳፭ ዓ.ም. በጉባኤ ኒቅያ ሲሰበሰቡ በኻያኛው ቀኖኗቸው የወሰኑት ቀኖና ነው /ሃይ.አበ.፳፡፳፮፣ The Oxford Dictionary of the Christian Church, pp 1250, 1738/፡፡ ይኽን ቀኖና ሲወስኑም ያለ ምክንያት አይደለም፤ ይኽ ወራት ከትንሣኤ ዘጉባኤ በኋላ ያለውን ሕይወታችን የሚያሳይ ስለኾነ ነው እንጂ፡፡ ከትንሣኤ ዘጉባኤ በኋላ ፈቃደ ሥጋን ለፈቃደ ነፍስ ለማስገዛት ተብሎ የሚደረግ ጦምም ኾነ ስግደት የለም፡፡ ሥጋ ሙሉ በሙሉ በዲያብሎስ ከመፈተን፣ ከእግዚአብሔር ውጪ የኾነ ሌላ ሐሳብን ከማሰብ ነጻ የሚወጣበት ወራት ነው፡፡ በዚያ ሰዓት ፈቃደ ሥጋ ከፈቃደ ነፍስ ጋር የተስማማ ነው፡፡ ሥጋ ሙሉ ለሙሉ ከድካሙ ነጻ ስለሚኾን እግዚአብሔርን ለማመስገን ትጉኅ ነው፡፡ እንደ አኹኑ እንቅልፍ እንቅልፍ አይለውም፤ ዘወትር የቅዱሳን መላእክትን ምግብ ለመብላት ማለትም ለማመስገን የተዘጋጀ ነው እንጂ፡፡

Friday, April 18, 2014

በዓለ ትንሣኤ

በገብረ እግዚአብሔር
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ ፲፩ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
የዚኽ ትምህርት መሠረታዊ ዓላማ ክርስቲያኖች ክርስቶስን መስለው እንዲነሡ ማበረታታት ነው፡፡
 በክርስትና ታሪክ፥ የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል ትልቁና ጥንታዊው ነው፡፡ በዓሉ በዓቢይ ጾም፣ በሰሙነ ሕማማት፣ በአክፍሎት እንዲኹም ከትንሣኤ እስከ ጰራቅሊጦስ ባለ የደስታና የሐሴት ወራት እንዲታጀብ መደረጉም ይኽን ታላቅነቱንና ጥንታዊነቱን የሚያስገነዝብ ነው፡፡ ምዕራባውያን ከትንሣኤ ይልቅ የልደትን በዓል በደመቀ አኳኋን ሲያከብሩ የምሥራቅ አብያተ ክርስቲያናት ግን ትንሣኤን ርእሰ በዓላት አድርገው ያከብሩታል፡፡

Wednesday, April 16, 2014

"ዘበተከ እምኔነ ኩሎ ማእሰረ ኃጣውዒነ በህማማቲከ ማኅየዊት ወመድኃኒት"


በክፍለ ሥላሴ
 (መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ 8 ቀን፣ 2006 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን


የኃይሉ ጥበብና ችሎታው ከፍጡራን ኅሊና በላይ የሆነ የቅዱሳን አምላክ ፈጣሪያችን ሰውን በፈቀደለት መንገድ እንዲመራና መንግስቱን እንዲወርስ የቅዱሳን እጆቹ የግብር ውጤት አድርጎ አበጀው:: ግና ህግን አፍርሶ በፈጣሪው ተከሶ እግዚአብሔር = አባቱን : ልጅነት= ሀብቱን : ገነት= ርስቱን..... ያጣው የሰው ልጅ መርገምን ወርሶ ቁርበት ለብሶ ወደ ምድር ተሰደደ:: በዚህ በሥጋ ከተፈረደበት የመቃብር ግዞቱ ላይ በሲኦል የነፍስ ርደት ስላገኘው የሞት ሞትን ሞተ እንላለን:: ቅዱስ ዳዊትም "ሰው ግን ክቡር ሆኖ ሳለ አያውቅም እንደሚጠፉ እንስሶች መሰለ።" (መዝ.48:12) ያለው የቀድሞ ክብሩን ከኋላ ግብሩ ጋር እያጻጸረ ሲያመለክተን ነው:: ይህንን የነቢዩን ቃል አብራርቶ የሚያስረዳ መልዕእክት በቅዳሴ አትናቴዎስ ላይ እናገኛለን እንዲህ ይላል ሊቁ "ሰብሰ እንዘ ንጉሥ ውእቱ ኢያእመረ" ዳዊት ክቡር ያለው የክብሩ መገለጫ ንግሥናው ነው ግን ያንን ያላወቀው የሰው ልጅ ምን እንዳገኘው ተመልከቱ "አህሰረ ርእሶ በፈቃዱ ወኮነ ገብረ ወመለክዎ እለ ኢኮኑ አጋእዝተ" አዎ ራሱን በፈቃዱ አሰረ ባርያ ሆነ መግዛት መፍጠርና ማስተዳደር ለባህሪያቸው የማይስማማቸውን የሚያመልክ ሆነ:: ከዚህ ጊዜ አንስቶ ለአምስት ሺህ ከአምስት መቶ ዓመታት የቀድሞ ጠላት ዲያቢሎስ ሰውን አስሮ "በግብርናት" የሚገዛው ሆነ::

Friday, December 6, 2013

“መምህር ሆይ! አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነኽ” /ዮሐ.፩፡፶/

በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፥ ኅዳር ፳፯ ቀን፥ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን የምታውቅ ነፍስ ሐሴት ታደርጋለች፡፡ ክርስቶስን፡- “አንተ መምህረ እስራኤል ነኽ፤ አንተ ንጉሠ ሰማይ ወምድር ነኽ” ትሏለች፡፡ ይኸውም እንደ ፊሊጶስ ማለት ነው /ዮሐ.፩፡፶/፡፡ ይኽቺ ነፍስ ሐሴትን የምታደርገው ግን በነቢብ ብቻ አይደለም፤ በገቢርም ጭምር እንጂ፡፡ ተወዳጆች ሆይ! ክርስቶስን ታውቁታላችሁን? እንኪያስ ትእዛዛቱን ጠብቁ፡፡ ክርስቶስን የሚያሳዝን ገቢር እየፈጸምን እንደምን ደስ የሚያሰኘውን ነገር ማድረግ ይቻለናል?

FeedBurner FeedCount