Saturday, October 4, 2014

ማኅሌተ ጽጌ፤ ምንጩ ትርጉሙና መልእክቱ (ክፍል አንድ)

በዲ/ ያረጋል አበጋዝ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መስከረም 25 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

 ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ኃይለ ቃልን ከትርጓሜ፣ ትርጓሜን ከምሥጢር እንዲሁም ደግሞ ምሥጢርን ከዜማ ጋር አስተባብረውና አስማምተው የሚደርሱ ሊቃውንት ባለቤት ናት፡፡ 5ኛው ..ዘመን የተነሣው ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ አምስቱን ጸዋትወ ዜማ ሲደርስ 14ኛው ..ዘመን የተነሣው አባ ጊዮርጊስ ደግሞ ሰዓታትን ደርሷል፡፡ በዚሁ ዘመን አባ ጊዮርጊስ ጋር ጥልቅ መንፈሳዊ ፍቅር የነበረው አባ ጽጌ ድንግልማኅሌተ ጽጌየተባለውን ድርሰት ደርሷል፡፡ ማኅሌተ ጽጌ ግጥማዊ አካሔድ ያለው ድንቅ ኢትዮጵያዊ ድርሰት ነው፡፡ ይህ ድርሰት በማንኛውም ጊዜ የሚጸለይ ቢሆንም በተለየ ሁኔታ በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የሚውለው ከመስከረም 26 እስከ ኅዳር 5 ቀን ድረስ ባለው የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የስደት ዘመን ነው፡፡ በዚህ ወቅት በየሳምንቱ እሑድ ሌሊት በሙሉ የእመቤታችንን ከልጇ ጋር ወደ ግብፅ መሰደድና መንከራተት እያሰቡ የሚደረስ ምሥጋናና ጸሎት ነው፡፡

Friday, October 3, 2014

ትምህርተ ሃይማኖት (ክፍል ሦስት)

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መስከረም 23 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ከኹሉም በፊት አንድ ኦርቶዶክሳዊ ክርስቲያን ማወቅ ያለበት
 አንድ ኦርቶዶክሳዊ ክርስቲያን ከኹሉም በፊት ስለ ነገረ ቤተ ክርስቲያን፣ ስለ ቅዱስ ትውፊት፣ ስለ ቅዱሳት መጻሕፍት የአተረጓጐም ስልት፣ ስለ ዶግማ እና ስለ ቀኖና በጥቂቱም ቢኾን ማወቅ አለበት፡፡ አስቀድሞ ከእነዚኽ መሠረታውያን ትምህርቶች ጋር የተዋወቀ ክርስቲያን በትምህርተ ሃይማኖት (ዶግማ) ውስጥ ለሚኖረው ትምህርት መሠረትን ይይዛል፡፡ የእነዚኽን ጽንሰ ሐሳብ ያልተረዳ እንደኾነ ግን ጭራሽኑ የክርስትናን ጽንሰ ሐሳብም ሊስተው ይችላል፡፡ የብዙዎች ከቤተ ክርስቲያን መጥፋትም በአንድም ይኹን በሌላ መልኩ የእነዚኽ ኦርቶዶክሳዊ ጽንሰ ሐሳቦች የዕውቀት ማነስ ነው፡፡ ኹሉንም አንድ በአንድ የምንመለከታቸው ሲኾን ለዛሬ ከነገረ ቤተ ክርስቲያን እንዠምራለን፡፡

Thursday, October 2, 2014

ሰላም ተዋሕዶ

በብጹዕ አቡነ ጐርጐርዮስ ካልዕ የሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የነበሩ


ሰላም ተዋሕዶ ሰላም ኦርቶዶክስ
የአትናቴዎስ ሐውልት የዲዮስቆሮስ፡፡
  የአዳም መመኪያ የሔዋን ሀገር
  አንቺ አይደለሽም ወይ የቅዱሳን ክብር?
በከንቱ የሞተው የአቤል መሥዋዕት
የኄኖክ ሃይማኖት የአዳንሽው ከሞት
አንቺ የኖኅ መርከብ የሴም በረከት፡፡
  በአብርሃም ድንኳን ተወልደሽ ያደግሽ
  የይስሐቅ መዓዛ ወደር የሌለሽ
  ያዕቆብ በሕልሙ በቤቴል ያየሽ
  የዮሴፍ አጽናኙ ተዋሕዶ አንቺ ነሽ፡፡

Wednesday, October 1, 2014

ዓምደ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
ርዕይ፡-
ሕፃናትና ወጣቶች የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያንን ሕግና ሥርዓት ዐውቀውና አክብረው በሃይማኖትና በምግባር ጸንተው ሲኖሩ ማየት፤

ተልዕኮ፡-

ለሕፃናትና ለወጣቶች ወንጌልን በማዳረስ ለቤተክርስቲያን ተተኪዎችን ማፍራት፤

ዓላማ፡-

ወቅቱን ያገናዘቡ መንፈሳዊ የማስተማሪያ ዘዴዎችን በመጠቀም ሕፃናትና ወጣቶች የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያንን ትምህርተ ሃይማኖት ሥርዓተ እምነትና ክርስቲያናዊ ትውፊት እንዲያውቁና እንዲጠብቁ ማስተማር፤

Tuesday, September 30, 2014

ለይሖዋ ምስክሮች ኑፋቄ የተሰጠ ምላሽ (ክፍል አንድ)

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መስከረም 21 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
  የይሖዋ ምስክሮች የተባለው ተቋም እ.ኤ.አ. በ1870 ላይ የተመሠረተ ሲኾን፥ መሥራቹም ፔንሳልቫንያ በምትባለው የአሜሪካ ግዛት እ.ኤ.አ. በ1854 ላይ የተወለደው ቻርለስ ራስል የተባለ ግለሰብ ነው፡፡ ይኽ ሰው ከጓደኞቹ ጋር በየጊዜው እየተገናኘ መጽሐፍ ቅዱስ ያጠና ነበር፡፡ የኋላ ኋላ ግን በተለያዩ የክሕደት ትምህርቶች ውስጥ ወደቀ፡፡ ከክሕደቶቹ መካከልም “ነፍስ ትሞታለች፤ ሥላሴ የሚባል ትምህርት የለም፤ ወልድ ፍጡር በመለኮቱ፤ ክርስቶስ በሥጋ አልተነሣም፥ በፍጹም ሥጋም ወደ ሰማይ አላረገም፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ሚካኤል ነው፤ ዘለዓለማዊቷ ገነት ይኽቺ የምንኖርባት ምድር ነች፤ ኃጢአተኞች ፈጽመው ከመኖር ወዳለመኖር ይጠፋሉ እንጂ የዘለዓለም ስቃይ የሚባል አያገኛቸውም፥ ሰይጣንም ቢኾን ወደአለመኖር ይጠፋል እንጂ አይሰቃይም፤ መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ኃይል እንጂ አካላዊ አይደለም” የሚሉ ይገኙበታል፡፡ ለዚኹ ትምህርቱ ይረዳው ዘንድም መጽሐፍ ቅዱስን በማጣመም “የአዲሲቱ ዓለም መጽሐፍ ቅዱስ” በማለት የራሱ የኾነ መጽሐፍ አዘጋጅቷል፡፡ በአኹኑ ሰዓትም ይኽን የክሕደት ትምህርታቸውን በተለያዩ ቋንቋዎች በማዘጋጀት ብዙ ሰዎችን እያታለሉ ይገኛሉ፡፡ እኛም፥ እግዚአብሔር በፈቀደልን መጠን፥ እነዚኽ ተረፈ አርዮሳውያን በትምህርተ ሥላሴ ዠምረን ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች አንድ በአንድ መልስ እንሰጥበታለን፡፡ ለዚኽም እግዚአብሔር ዓይነ ልቡናችንን ያብራልን፤ አሜን!!!

Monday, September 29, 2014

ሥነ ፍጥረት (ለሕፃናት)- ክፍል ኹለት



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መስከረም 19 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
 እንደምን ናችኁ ልጆች? ትምህርት በደምብ ዠመራችኁ? እንዴት ነው ታድያ ትምህርት? በጉጉት እየተከታተላችኁ ነው አይደል? ጐበዞች፡፡ አኹን የምትማሩት ትምህርት ለወደፊት ኑሮአችኁ መሠረት በመኾኑ ተግታችኁ ተማሩ፤ እሺ?! እግዚአብሔር ብርታትን እንዲሰጣችኁ፣ የእናንተንና የቤተ ሰቦቻችኁ ጤንነት እንዲጠብቅላችኁም ዘወትር ጸልዩ፡፡ እግዚአብሔር ጸሎታችኁን እንዲሰማችኁም ለወላጆቻችኁና ለታላላቆቻችኁ በቅንነት ታዘዙ፡፡ ይኽን ካደረጋችኁ፥ ዕቅዳችኁና ምኞታችኁ ይሳካላችኋል፡፡
 ልጆች! ባለፈው ሳምንት የተማርነውን ታስታውሳላችኁ? እስኪ ምን ምን ተማርን? ጐበዞች!!! ጥያቄውንስ ሠራችኁት? ስንት አመጣችኁ? እናንተ ጐበዞች ስለኾናችሁ ደፍናችኁታል አይደል? በጣም ጐበዞች፡፡ ለዛሬ ደግሞ እግዚአብሔር ረቡዕ፣ ሐሙስ እና ዓርብ ምን ምን እንደፈጠረ እንማራለን፡፡ እግዚአብሔር ልቡናችንን ይክፈትልን፡፡ አሜን!!!

Tuesday, September 23, 2014

ትምህርተ ሃይማኖት (ክፍል ኹለት)

 (መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መስከረም 13፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

የሃይማኖት አዠማመርና ዕድገት

 የተለያዩ ሰብአ ዓለም (የዚኽ ዓለም ሰዎች) የሃይማኖት አመጣጥን በተመለከተ የተለያየ ዓይነት አመለካከት ቢኖራቸውም፥ እኛ ኦርቶዶክሳውያን ግን ሃይማኖት ገና ከፍጥረት መዠመሪያ (ከዓለመ መላዕክት) ዠምሮ የነበረ መለኮታዊ ስጦታ ነው ብለን እናምናለን /ሐዋ.17፡26/፡፡ የመዠመሪያዎቹ ምእመናንም ቅዱሳን መላዕክት ናቸው፡፡ ይኽ እንዴት እንደኾነም በሥነ ፍጥረት ትምህርታችን የምንመለስበት ይኾናል፡፡
ከቅዱሳን መላዕክት በኋላ ይኽቺው ነቅዕ፣ ኑፋቄ የሌለባት ንጽሕት ሃይማኖት አዳምና ሔዋን በተፈጠሩ በ40 እና በ80 ቀናቸው ተቀብለዋታል፡፡

Monday, September 22, 2014

ሥነ ፍጥረት (ለሕፃናት)



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መስከረም 12 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ልጆች እንደምን ከረማችኁ? የዕረፍት ጊዜአችኁ እንዴት አለፈ? መልካም ልጆች፡፡ እንግዲኽ ዘመነ ማርቆስ አልፎ አኹን ዘመነ ሉቃስ ገብተናል፡፡ ለአዲሱ ዓመት ያደረሰንን አምላክ እያመሰገንን በዚኽ ዓመት ደግሞ ጊዜያችንን በአግባቡ ተጠቅመን፣ በትምህርታችንም በርትተን ለጥሩ ውጤት መብቃት አለብን እሺ፡፡ ምክንያቱም ጊዜውን በአግባቡ የማይጠቀም ልጅ መጨረሻው አያምርም እሺ ልጆች፡፡ ስለዚኽ ጊዜአችንን በአግባቡ መጠቀም አለብን፡፡ ለዚኽም እግዚአብሔር ይርዳን፡፡

Friday, September 19, 2014

"እርግና"



በዲ/ን ዶ/ር ቴዎድሮስ በለጠ


(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መስከረም 9 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

የእድሜ ጅራፍ ግርፋቱ = ከግንባሬ
የክብር ሸማ ሽበቱ = ከጠጉሬ
የአዝማናት ፍኖት ንቃቃት = ተረከዜ
የምድር ሩጫ ሥጦታ = "ደም- ወዜ"
ለቁጥር መሳፍርት = ብልጥግና
ዳግም ለንሰሃ ............ ዳግም ለምስጋና
ጊዜ ለእርጋታ..... ጊዜ ለጥሙና
ፍፃሜ መዋዕል ......... ድህረ ውርዝውና

Monday, September 15, 2014

የትምህርተ ሃይማኖት መግቢያ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መስከረም 5 ቀን፣ 2007 ..)- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
 “ሃይማኖትማለት አምነ፣ አመነ ከሚል የግእዝ ግሥ የወጣ ሲኾን መዝገበ ቃላታዊ ትርጓሜውምማመን፣ መታመንማለት ነው፡፡ በምሥጢራዊው ትርጕሙ ግንሃይማኖትማለት ፍጥረትን ኹሉ ካለ መኖር ወደ መኖር ያመጣ አንድ እግዚአብሔር እንዳለ፣ ለሚታየውም ለማይታየውም ፍጥረት ሠራዒውና መጋቢው ርሱ ብቻ እንደኾነ፣ ልዩ ሦስትነት እንዳለው፣ በዚኽ አለ በዚኽ የለም የማይባል ምሉዕ በኵለሄ እንደኾነ፣ማመን መታመን ማለት ነው፡፡

Tuesday, September 9, 2014

ዘመኔን አድሰው


በወርቅነሽ ቱፋ
ይኸው
ሩቅ ያልኩት ቀረበ፥ ነገ ዛሬ ሊኾን፥ መጣ እየበረረ፤
በለስ ሕይወቴም ሲፈተሸ፥ ምንም አላፈራ፥ አላዘረዘረ፡፡

Sunday, September 7, 2014

አዲሱ ዓመት - ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዳስተማረው (የመጨረሻው ክፍል - ክፍል ፬)



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ጳጉሜ ፪ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
የቀጠለ…
 እግዚአብሔር የሚወዳችኁ እናንተም የሚምትወዱት ልጆቼ! ይኽን ኹሉ በዝርዝር የምነግራችኁ ለምን ይመስላችኋል? ይኽን ኹሉ በዝርዝር መናገሬ በዘዴ ኹላችንም የምናደርገውን ማናቸውም እንቅስቃሴያችን ለእግዚአብሔር ክብር እናደርገው ዘንድ ስለምሻ ነው፡፡ በባሕር የሚነግዱ ነጋዴዎች ንብረታቸውን ወደ ከተማ ዳር መልሕቅ ካመጡ በኋላ መዠመሪያ የሚያደርጉት ነገር ቢኖር በቀጥታ ወደ ገበያ ሥፍራ መሔድ አይደለም፡፡ ወደ ገበያ ሥፍራ ከመሔዳቸው በፊት ስለ ትርፋቸው ያስባሉ እንጂ፡፡ እኛም በምናደርገው ኹሉ ከእግዚአብሔር ዘንድ የምናገኘውን ጥቅም ማሰብ አለብን፡፡

Saturday, September 6, 2014

አዲሱ ዓመት - ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዳስተማረው (ክፍል ፫)



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ጳጉሜ ፩ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
የቀጠለ…                       
 ለእግዚአብሔር ክብር ብሎ ሰውን መውቀስም አለ፡፡ ከእናንተ መካከል፡- “እንዴት ብሎ? ርግጥ ነው ብዙውን ጊዜ ሠራተኞቻችንን እንወቅሳለን፡፡ ለእግዚአብሔር ክብር ብሎ መውቀስስ እንደምን ያለ ነው?” አዎ! የሚሰክር ወይም የሚሰርቅ ሠራተኛ ወይም ጓደኛ ብናይ ወይም ከዘመዳችን አንዱ ወደ ተውኔት ቤት፣ ወይም ለነፍሱ ምንም ረብሕ ወደማያገኝበት ሥፍራ ሲሮጥ፣ በከንቱ ሲምል፣ የሐሰት ምስክርነትን ሲሰጥ፣ ወይም ሲዋሽ፣ ወይም ሲቈጣ ብናየው ዠርባችንን ብንሰጠውና ብንገሥፀው ወቀሳችን ለእግዚአብሔር ክብር የተደረገ ነው ይባላል፡፡

Tuesday, September 2, 2014

አዲሱ ዓመት - ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዳስተማረው (ክፍል ፪)




(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ነሐሴ ፳፯ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
የቀጠለ…

 ከገቢረ ኀጢአት ሳይወጡ አዲስ ዓመት ሲመጣ መደሰት፣ ብዙ መብልና መጠጥ ማዘጋጀት፣ አዲስ ልብስም መልበስ ጥቅም የለውም፡፡ ነፍሳችን በኀጢአት እየተጨነቀች፣ ነፍሳችን ተርባና ተጠምታ ሳለ፣ የተዳደፈ የኀጢአት ልብስም ተጆቡና ሳለ አዲስ ዓመት ማክበር ለእኛ ምን ጥቅም ይሰጠናል? እንዲኽ ከገቢረ ኀጢአት ሳይወጡ አዲስ ዓመትን ማክበር ማለት ለእኔ እንደ ልጆች የዕቃ ዕቃ ጨዋታ ነው፡፡

Saturday, August 30, 2014

አዲሱ ዓመት - ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዳስተማረው (ክፍል ፩)



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ነሐሴ ፳፬ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
 የምወዳችኁ ልጆቼ! አዲሱ ዓመት የደስታ የሰላምና የጤና እንዲኾንላችኁ ትሻላችሁን? እንኪያስ ገና ከዥመሩ በስካር፣ በዘፈን፣ በገቢረ ኀጢአት ለማሳለፍ አታቅዱ፡፡ የአዲሱ ዓመት የመዠመሪያውን ዕለት ብቻ ሳይኾን እያንዳንዱን ቀን በገቢረ ኀጢአት አትዠምሩት፡፡ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ሥራ፣ ምግባር ትሩፋት በመሥራት አሐዱ በሉ እንጂ፡፡ ዕለታት ክፉዎች ወይም ጥሩዎች የሚኾኑት በተፈጥሮአቸው እንደዚያ ኾነው አይደለም፡፡ ዕለቱን ክፉ ወይም ደግ እንዲኾን የምናደርገው እኛው ነን፡፡ የአምናው ማግሰኞ ከዘንድሮ ማግሰኞ የተለየ አይደለም፡፡ የተለየ የሚያደርገው የእኛ ብርታት ወይም ስንፍና ብቻ ነው፡፡

Tuesday, August 12, 2014

ማርያም ፊደል

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ነሐሴ ፯ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
 እንኳን ለዓለም ኹሉ ደስታን ወዳመጣችው ዕለት አደረሳችኁ፤ አደረሰን፡፡ ነሐሴ ሰባት ቀን የባሕርያችን መመኪያ የምትኾን ንጽሕተ ንጹሐን፥ ቅድስተ ቅዱሳን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተፀነሰችበት ዕለት ነው፡፡ ይኽቺን ዕለት ያልናፈቀ ትውልድ የለም፡፡ ጽድቃቸው እንደ መርገም ጨርቅ ለኾነባቸው ቅዱሳን አበው ወእማት ተስፋቸው የሚፈጸመው በዛሬው ዕለት በተጸነሰችው በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ነውና፡፡ ቅድስትና ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያናችንም ከእግዚአብሔር ቀጥሎ እንደ እመቤታችን ከፍ ከፍ የምታደርገው ፍጥረት የሌለው ስለዚኹ ነው፡፡ ሊቃውንቱ፡- “ሐና አንቺን የጸነሰችበት የደስታ ቀን ምን ያኽል የተባረከች የተቀደሰች ቀን ናት፤ ሟች ኢያቄምም ለሕይወት አንቺን  ያፈራባት ቀን ምን ያኽል የተባረከች የተቀደሰች ቀን ናት፤” ብለው የሚዘምሩላትም ይኽን ምሥጢር በልቡናቸው ቋጥረው ነው /አባ ጽጌ ድንግል፤ ማኅሌተ ጽጌ ቁ.፵፬/፡፡

Monday, August 4, 2014

መቅረዝ ዘተዋሕዶ - የውዳሴ ማብራርያ መጽሐፍ በገበያ ላይ ዋለች



መቅረዝ ዘተዋሕዶ ከዚኽ በፊት ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ባዘጋጁት የትርጓሜ መጽሐፍ ተተንተርሳ የተዘጋጀች መጽሐፍ ስትኾን የምትለየውም፡-
፩ኛ) የጥንቱን ለዛ ሳትለቅ ቀለል ባለ አቀራረብና ይዘት በእያንዳንዱ ምዕመን እጅ እንድትደርስ በማሰብመዘጋጀቷ፤
፪ኛ) “እንዲል፣ እንዳለ፣ እንዲሉየሚለውን ጥንታዊ አቀማመጥ ጸሐፊውንና ደራሲውንመለየቷ፤
፫ኛ) አንዳንድ ተጨማሪ ማብራርያ የሚያስፈልጋቸውን ምንባባት ከተለያዩ ድርሳናት ተጨማሪ ማብራሪያመያዟ፤
፬ኛ) የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ በሚያስፈልጋቸው ቦታዎች ላይ ጥቅሱን በማስቀመጥ ምዕመናን እንዲያመሳክሩት መንገድመክፈቷ ነው፡፡

FeedBurner FeedCount