Friday, October 26, 2012

ቅዱስ እሰጢፋኖስ

               በዲ/ ሽመል መርጊያ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
  
 በሐዋርያት ስብከት ቤተ ክርስቲያን ስትስፋፋ በትምህርታቸውና በተአምራታቸው ተስበው ወደ ክርስትና እምነት የተመለሱ ከአይሁድና ከአሕዛብ ወገን የሆኑ ክርስቲያኖች መሬታቸውንና ጥሪታቸውን በመሸጥ  ያላቸውን ሀብት አንድነት በማድረግ በኢየሩሳሌም የአንድነት ኑሮን ይኖሩ ነበር፡፡ በኅብረትም የሐዋርያት ትምህርትን በመስማትና  በጸሎት ይተጉ እንዲሁም ማዕድን በመባረክ በጋራ ይመገቡ ነበር፡፡ መጽሐፍ ቅዱስምአንድ ልብና አንዲት ነፍስ አላቸው በማለት (የሐዋ.432) ስለአንድነታቸው ፍጹምነት ይነግረናል፡፡

Tuesday, October 23, 2012

ሞትን መፍራት ማቆም የሚቻለው እንዴት ነው?



በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
 
ጥያቄ፡- እሞታለሁ ብዬ ሳስብ በጣም እጨነቃለሁ፡፡ እናቴ እንደነገረችኝ ከሆነ ሞትን መፍራት የጀመርኩት ገና ከልጅነቴ ጀምሬ ነው፡፡ አሥራ ሁለተኛ ክፍል ሳለሁ በጣም ከምቀርባቸው ጓደኞቼ መካከል ከአንዱ ጋር ተጣላሁና ሳልታረቀው በሳምንቱ ሞተ፡፡ በጊዜው በጣም ጸጸተኝ፡፡ ሞትን ባሰብኩ ቁጥር የሚታየኝ ያ ሳልታረቀው የሞተው ልጅ ነው፡፡ የመፍራቴ መጠንም በእድገቴ ልክ እየጨመረ ነው፡፡ ሌሊት ላይ ባንኜ “አሁን ብሞትስ?” ብዬ እጨነቃለሁ፡፡ ንስሐ ብገባም ፍርሐቱ ሊለቀኝ አልቻለም፡፡ “ሰው ሞተ” ሲባልም በጣም እደነግጣለሁ፡፡ የምደነግጠውና የምፈራው ግን ሰውዬው ስለሞተ ሳይሆን “እኔም እኮ እሞታለሁ” ብዬ ነው፡፡ እባካችሁ በጣም ጨንቆኛልና ሞትን መፍራት ማቆም የሚቻለው እንዴት ነው?
                             እኅታችሁ ኤልሣቤጥ ነኝ ከአ.አ. 

ምላሽ፡-ውድ ጠያቂያችን! የእግዚአብሔር ፍጹም ሰላምታ ባለሽበት ይድረስሽ፡፡ ለጠየቅሽን ጥያቄ የቻልነውን ያህል ለመርዳት መጻሕፍተ ሊቃውንትን አገላብጠን ያገኘነውን መልስ እነሆ ብለናል፡፡ እንደ ጠቋሚ ይረዳሻል ብለንም እናምናለን፡፡ ከቻልሽ አስቀድመሽ በጸሎት ጀምሪና በተመስጦ ሆነሽ አንቢው፡፡ መልካም ንባብ!

ከማኻ ዝበለ መሓሪ መን እዩ?


በስመ ኣብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኣሓዱ ኣምላክ ኣሜን!

ናይዛ ትምህርቲ እዚኣ ቐንዲ ዕላማ ኩላትና ምሕረት ምግባር ንኽንለማመድ ምትብባዕ እዩ፡፡
ነዚኣ ቃል እዚኣ ዝተዛረባ ማኅሌታይ ኣቦና ቅዱስ ያሬድ እዩ፡፡ ቅዱስ ያሬድ ምሕረት እግዚኣብሄር ኣብ ብሉይ ኪዳን ብዕምቆት እንዳስተንተነ የመስግን፤ ይዝምር ከኣ፡፡ ኣስፍሕ ኣቢሉ ክገልፆ እንተሎ “ቃል ኪዳንካ ምስ ኖህ ዘፅናዕካ፣ ንእስራኤላውያን ካብ ሰማይ ማና ኣውሪድካ ዝመገብካ፣ ንምድሪ ጽጌሬዳ ዕንበባን ፍርያትን ሂብካ ፍጥረት ኩሉ እትምግብ፣ ንሰማይን ምድርን ዝፈጠርካ፣ ኩሉ ፍጥረት ብተስፋ ንኣኻ ዝጽበ ከማኻ ዝበለ መሓሪ መን እዩ?” ይብል፡፡ ዋላ ሓደ!

ምሕረት ማለት ቅፅዓት ንዝግብኦ ገበነኛ ርህራሄ ምግባር እዩ /መዝ.51፡1፣7-8/፡፡ ፍቱዋት! ከም ኣበሳና እንተንፍደ ከምቲ ቅፅዓት ዝግበኣና ከኣ እንተንኽፈል ነይርና ኣብ ሓንቲት ሰዓት ጥራይ ክንደይ ጊዜ ምሞትና? እስቲ ካብ ዝወግሕ ጀሚሩ ክሳብ እዛ ሕጂ ዘለናያ ደቒቓ ጥራሕ ክንደይ ግዘ አበስና? እሞ ኣምላኽናኸ ክንደይ ግዘ ሓለፈና? ልቢ ኣምላኽ ዳዊት ነዚ እንዳስተንተነ እንትዝምር ከምዚ ይብል፡- “እግዚኣብሄር ርህሩህን መሓርን እዩ፤ ንኹራ ደንጓዪ፤ ብምሕረት ድማ ምሉእ እዩ፡፡ መግናሕቱ ንግዚኡ እዩ፤ ንዘልኣለም ከኣ ኣይቕየምን እዩ፡፡ ከም መጠን ሓጢኣትና ኣይቀፅዓናን እዩ፤ ከም መጠን አበሳና ድማ ኣይፈድየናን እዩ፡፡ ሰማይ ካብ ምድሪ ልዕል ከም ዝብል ከምኡ ምሕረቱ ኣብ ልዕሊ እቶም ዝፈርሕዎ ዓብዪ እዩ፡፡ ምብራቕ ካብ ምዕራብ ከም ዝርሕቕ ከምኡ ኣበሳና ኻባና ኣርሐቐ” /መዝ.103፡8-12/፡፡ 

እግዚኣብሄር ወልድ ኣብ ደንበ ማል ዝተወልደ፣ ገና ብዕሸሉ እንተሎ ኣብ ሕቑፊ ኣዲኡ ዝተሰደደ፣ በኳሩ እኳ መሕደሪ ጕድጓድ እንዳሃለወን ንሱ ግና ርእሱ ዘፅግዓላ እንተይሃለዎ ከርተት ዝበለ፣ ኣብ መስቀል ዕርቃኑ ወፂኡ ስሌና ዝሓመመን ዝተሳቐየን፣ ብመወዳእትኡ ከኣ ብኣሰቃቒ ሞት ዝሞተ ንዓለም ብምልኡ ምሕረት ክገብረሉ ስለ ዝፈተወ እዩ /ኤፌ.2፡4-5፣ 1ጴጥ.1፡3፣ ሮሜ.5፡6-10/፡፡ ናይ ኣምላኽ ምሕረቱ ካብ ሕሊና ሓሳብ ኩሉ ዝበዝሕ እዩ /ዘኅ.14፡18/፤ ክሳብ ሰማያት ዝበፅሕ ሰፊሕ እዩ

Thursday, October 18, 2012

ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ


  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

 ባለፈው ዝግጅታችን ስለቅዱሳን ሐዋርያት አጠቃላይ መግቢያ አቅርበን በቀጣይነት ደግሞ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የእያንዳንዱን ሐዋርያ የተጋድሎ ሕይወት በዝርዝር እንደምናቀርብ ቃል ገብተን ነበር (የባለፈውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ በመሆኑም ለዛሬ የሐዋርያት አለቃ የሆነውን የሐዋርያው የቅዱስ ጴጥሮስን ሕይወትና ተጋድሎ እነሆ ብለናል መልካም ንባብ።

Tuesday, October 16, 2012

አብርሃም ሳይወለድ እኔ አለሁ- የዮሐንስ ወንጌል የ 39ኛ ሳምንት ጥናት


(ዮሐ.8፡48-59)

  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

ክፋትን የሚሠራት ሰው በጣም የባሰና አሳፋሪ የሚያደርገው ተሸማቅቆና አፍሮ ራሱን መደበቅ ሲገባው ይባስኑ ለስሕተቱና ለክፋቱ ምክንያትን እየፈለገ ሲቀጥልበት ነው፡፡ አይሁዳውያንም እንዲህ ዓይነት ሰዎች ነበሩ፡፡ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “እናንተ የአብርሃም ልጆች አይደላችሁም፡፡ የአብርሃምስ ልጆች ብትሆኑ የአብርሃምን ሥራ በሠራችሁ ነበር፤ ከአብ ዘንድ በሕልውና ያየሁትንና የሰማሁትን እውነቱን የምነግራችሁ እኔን ልትገድሉኝ ትሻላችሁና፡፡ አብርሃም እንዲህ አላደረገም፤ ነፍስ አልገደልም፡፡ መግደልስ ይቅርና ልጁን ነበር ለእግዚአብሔር የሠዋው፡፡ ነፍስስ መግደል ይቅርና የወጣው የወረደውን፣ ያለፈው ያገደመውን እንግዳ ነበር ሲቀበል የነበረው፡፡ እንኳንስ እንዲህ ያለ ትምህርት አግኝቶ ነግረውትና አስተምረውት አላምንም ማለት ይቅርና ወጥቶ ወርዶ ነበር ፈጣሪውን ያገኘው፡፡ ስለዚህ እናንተ ልትገድሉኝ እንደምትሹ አባታችን የምትሉት አብርሃም እንዲህ አላደረገም፡፡ በዚያም ላይ ደግሞ ባስተምራችሁ አልተቀበላችሁኝም፡፡ ስለዚህ የአባታችሁኝ የሰይጣን ሥራን ትሠራላችሁና አባታችሁ አብርሃም አይደለም፡፡ እናንተስ ከእግዚአብሔር አይደላችሁም” ብሎ ማየት ያቃታቸውን የመረቀዘ ቁስላቸውን ቢያሳያቸው የባሰ ተናደዱ (ይህን የበለጠ ለማንበብ እዚህይጫኑ)፡፡ በቁስላቸው ላይ ጨው ጨመሩበት፤ “አንተ በእውነት ሳምራዊ ነህ (አይሁዊ አይደለህም) የምንልህ ስለዚሁ አይደለምን? ጋኔን አድሮብሃል፤ የእግዚአብሔር ልጅ አይደለህም የምንልህስ በዚህ ምክንያት አይደለምን?” ብለው ከወገንነት አውጥተው ከይሁዲነት አግልለው ሰደቡት /ቁ.48/፡፡ እንደ እነርሱ አስተሳሰብ ሳምራዊ ማለት የተናቀ፣ የሚለውን የማያውቅና እንዲሁ የሚዘባርቅ፣ ከአይሁድ ጋር የማይተባበር ይልቁንም የአይሁድን እምነት የሚያናንቅ ነው፡፡ በዚህ አነጋገራቸው ጌታችን ጸረ አይሁድ አቋም እንዳለው አስመስለው ለማቅረብም ሞክረዋል፡፡ አይሁድ ሆይ! ጋኔን ያደረበት ማን ነው? እግዚአብሔርን የሚያከብር ወይስ እግዚአብሔር አብን ያከበረው ወልድን የሚሳደብ? /St. John Chrysostom, Homily 55/፡፡


Monday, October 8, 2012

ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ ግብጽ ሽሽ


   በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

የዚህ ትምህርት መሠረታዊ ዓላማ ክርስቲያኖች ከጌታችንና ከእመቤታችን ስደት በረከት ተሳታፊዎች እንዲሆኑ ማድረግ ነው፡፡ ቀዳማዊ አዳም የማይበላ በልቶ በራሱና በልጆቹ የሞት ሞት ተፈረደበት፤ ጸጋ እግዚአብሔር ጎደለበት፤ የሚሠዋው መሥዋዕት የሚጸልየው ጸሎት ግዳጅ የማይፈጽም ሆነበት፡፡ ምድር ከእርሱ የተነሣ እሾክና አሜከላ አበቀለችበት፡፡ 

ሆኖም (አዳም) ምንም ባልበደለው ሰይጣን እንዲሁ ቢሞትም የተበደለው አምላኩ ግን እንዲሁ ሕይወትን ይሰጠው ዘንድ ወደደ፡፡ (አዳም) አምላክ መሆንን ሽቶ ነበርና ይህን ይሰጠው ዘንድ (አምላክ) ዳግማይ አዳም ይሆንለት ዘንድ ወደደ፤ አስቀድሞ ከነበረው ክብር በላይ ሌላ ክብር ይጨምርለት ዘንድ ፈቀደ፡፡ ጊዜው ሲደርስም አካላዊ ቃል ንጹሕ የሆነ ባሕርዩን (የእመቤታችን ሥጋና ነፍስ) ነሥቶ ዝቅ ያለውን ከፍ ያደርገው ዘንድ ዝቅ አለለት፤ የጸጋ ልብሱን ይመልስለት ዘንድ የማይዳሰስ እርሱ በጨርቅ ተጠቀለለት፤ ወደ ክብሩ ይመልሰው ዘንድ በርካሽ ቦታ ያውም በግርግም ተወለደለት፡፡

Kadhata Sa’aatii Sadii


Maqaa Abbaa kan Ilmaa kan Afuura Qulqulluu Waaqa Tokko Ameen!

Faaruu 129

Yaa Waaqayyoo ani qilee keessa ta’een si waammadhe.
Sagalee koo naaf dhagayi;
gurri kee sagalee kadhannaa kootii kan dhaga’u haata’u.
Yaa Waaqayyoo osoo ati cubbuu namaa sakattaatee eenyuutu dhaabbataa?
Garuu dhiifamni si bira jira.
Kanaaf sababa maqaa keef abdiin si godhadhe;
lubbuun koo seera keetiin obsite.
Sa’atii barii irraa eegalee hanga
halkaniitti lubbuun koo Waaqayyoon amane.
Waaqayyo biraa haraara
isa biras fayyina hedduutu jira.
Innis Isiraa’eeliin cubbuu isaa mara irraa isa fayyisa.
Abbaa Ilma Afuura Qulqulluuf galanni haa ta’u bara baraan Ameen!

Thursday, October 4, 2012

ነገረ ማርያም- ክፍል ፩ (መግቢያ)



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ታኅሳስ ፩ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

  
  ይህ የነገረ ማርያም (Mariology) ትምህርት ስለ እመቤታችን ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም ከፅንሰቷ ጀምሮ እስከ ዕርገቷ ስላለው የሕይወቷን ዝክረ ታሪክ፣ ስለ እመ አምላክነቷ፣ ስለ ዘላለማዊ ድንግልናዋ፣ በነገረ ሥጋዌ ስላላት ሱታፌ (ድርሻ)፣ ስለ ንጽሕናዋና ስለ ተሰጣት ክብር የምናጠናበት የሃይማኖት ትምህርት ክፍል ነው፡፡

Wednesday, October 3, 2012

በቃሌ ብትኖሩ በእውነት ደቀመዛሙርቴ ናችሁ


    የዮሐንስ ወንጌል የ38ኛ ሳምንት ጥናት (ዮሐ.8፡21-47)
  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
 (ከቻሉ ጸልየው ይጀምሩ)
  ልበ ስሑታን የሆኑ ጸሐፍትና ፈሪሳውያን ጌታችንን ለመግደል፣ ከሕዝቡ ልብ ለማውጣት ያልፈነቀሉት ድንጋይ ያልፈለጉበት ስሕተት የለም፡፡ ሆኖም ንጹሐ ባሕርይ ነውና ይህን ያገኙበት ዘንድ አልተቻላቸውም፡፡ እግዚአብሔር ነውና በልባቸው የሚያመላልሱትን ስለሚያውቅ ኃጢአታቸውን አውቀው ፍቅሩን እንዲረዱለት፤ የታመሙትን (እነርሱን) ፍለጋ እንደመጣ እንዲያውቁለት በጥበብ፣ በኃይል እንዲሁም በሥልጣን ይነግራቸው ነበር፡፡ አንዳንድ ጊዜ በሚያስፈራሩ ቃላት ሌላ ጊዜም በሚጋብዙ የትሕትና ቃለት ያምኑበት ዘንድ ይጠራቸው ነበር፡፡ እነርሱ ግን ይህን እንዳያውቁ በምርጫቸው ልባቸውን አደንድነውታልና ይገድሉት ዘንድ ፈለጉ፡፡

Sunday, September 30, 2012

ከሰው ይልቅ እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት


አባታችን ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ በጊዜው የነበረችው ጨካኝ ንግሥት (ኤውዶክስያ) በክፋት ተነሣስታ በመንፈቀ ሌሊት አስጠርታ በፈረስ በሠረገላ አድርጋ ወደ ደሴተ አጥራክያ ስታግዘው ለራሱ እንዲህ አለ፡- ንግሥቲቱ ከከተማ ስታስወጣኝ ምንም ዓይነት ንዴት አልተሰማኝም፤ ይልቁንም ለራሴ እንዲህ አልኩ እንጂ፡-

Thursday, September 27, 2012

የዕርቅ ቀን


    በእግረ ሕሊናችሁ ከአዲስ አበባ በሰሜን አቅጣጫ 1010 ኪ/ሜ ልውሰዳችሁ፡፡ የጠቀስኩላችሁን ያህል ርቀት ስትጓዙ ዓድዋ ከተማ ትደርሳላችሁ፡፡ ዓድዋ ማለት “ኦድዋ” ከሚል የግእዝ ግስ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም ከበብዋት ማለት ነው፡፡ ከተማዋ ይህን ስም ያገኘችው ዙርያዋ በተስዓቱ ቅዱሳን ገዳማት የተከበበች ስለሆነ እንደሆነ ይነገራል፡፡ አጠገብዋም ዓዲ አቡን - የአቡን ሀገር የምትባል ሌላ ከተማ አለች፡፡ እዚያ አከባቢ ብቻ የሚበቅል ቲማቲም መሰል አትክልት አለ፡፡ ስሙም “ጸብሒ አቡን” ይባላል፡፡ የአቡን ወጥ እንደማለት ነው፡፡

Wednesday, September 26, 2012

መስቀል ኃይላችን ነው



ከጌታችን ስቅለት በፊት መስቀል መቅጫ ነበር፡፡ ሰውን በመስቀል መስቀል የጀመሩት ፋርሳውያን ናቸው፡፡ እነዚህ ሰዎችኦርሙዝድየሚባል የመሬት አምላክ ስለበራቸው እርሱን ላለማርከስ ብለው ወንጀለኛውን ሁሉ ከመሬት ከፍ አድርገው ሰቅለው ይቀጡት ነበር፡፡ በኋላም ይህ አድራጎት በሮማውያን ግዛት ሁሉ ሕግ ሆነ፡፡
በኦሪቱ ሥርዓትም በመስቀል የሚቀጡ ርጉማን ውጉዛን ነበሩ፡፡ ከጌታችን ስቅለት በኋላ ግን የነጻነታችን አርማ የድል ምልክታችን ሆነ፡፡ ክርስቶስ ይህን መስቀል ዙፋኑ አድርጎ ሰላምን እኩልነትን አድርጓልና፡፡ ስለዚህ ካሉን ነገሮች ሁሉ መስቀል የላቀ ክብር አለው፡፡

Monday, September 24, 2012

MESKEL IN ETHIOPIA



In The Name of The Father, The Son; & The Holy Spirit One God Amen!!

The word Meskel has two meanings. One literal meaning is the Holy Cross. The other meaning is the Feast of the Holy Cross; an event which is annually celebrated in Ethiopia in commemoration of the finding of the Holy Cross. The Holy Cross is very significant in the Ethiopian Orthodox Tewahdo Church (EOTC). The founding father of EOTC hymn, St. Yared, says in his composition hymn book ‘MERAF’ that the Holy Cross is above everything else in the Church. He says ‘It saves us from our enemy; the devil. It is true that the Holy Cross has saved the entire world.’

Wednesday, September 19, 2012

ምክረ አበው -ቁጥር ሦስት


1. ከዕለታት በአንድ ቀን አባ ፓምቦ አባ እንጦንስን “ማድረግ ያለብኝ ነገር ምንድነው?” ብሎ ይጠይቋል፡፡ አባ እንጦንስም እንዲህ ሲል መለሰለት “በራስህ ጽድቅ አትታመን፤ ላለፈው አትጨነቅ፤ ይልቁኑ አንደበትህንና ሆድህን ግዛ፡፡”
2. አባ እንጦንስ በአንድ ወቅት እንዲህ አለ፡- “በዚህች ምድር ላይ ስንኖር ሕይወታችንንም ሆነ ሞታችን ከባልንጀራችን ጋር ነው፡፡ ወንድማችንን ገንዘብ ካደረግነው እግዚአብሔርን ገንዘብ እናደርጓለን፤ ወንድማችንን ካስቀየምነው ግን በክርስቶስ ላይ ኃጢአትን እንሠራለን፡፡”

Sunday, September 16, 2012

እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ


  የዮሐንስ ወንጌል 37 ሳምንት ጥናት (ዮሐ.812-20)

     በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

  በምንዝር በያዝዋት ሴት ላይ ለመፍረድ ተሰብስበው የነበሩት አይሁድ ፈሪሳውያን ጌታችን ጸሐፍት ፈሪሳውያን ሆይ! ኃጢአታችሁ ከዚህች ሴት ኃጢአት የባሰ እንደሆነ ተመልከቱ፡፡ ታውቁት ትረዱት ዘንድም አሁን ሕሊናችሁን መርምሩ፡፡ ስለዚህ እናንተው ራሳችሁ ወንጀለኞች ሳላችሁ በዚህች ሴት ላይ የምትፈርዱ አትሁኑ፡፡ ይልቁንም እርሷን ከመውቀሳችሁና ከመክሰሳችሁ በፊት ራሳችሁን የምትወቅሱ ሁኑ፡፡ እርሷ ተወግራ እንድትገደል የምትፈርዱ ከሆነ ግን እናንተም ከዚያ ነጻ አይደላችሁምብሏቸው እነርሱም ይህን ዘለፋ በሰሙ ጊዜ ሕሊናቸው ወቅሷቸው በፊት ከገቡት ጀምሮ በኋላ እስከ ገቡት ድረስ አንድ አንድ እያሉ እየወጡ ሄደው ነበር /.9/፡፡(በዚህ እስ ላይ ይህን ይመልከቱ እኔም አልፈርድብሽም- የዮሐንስ ወንጌል የ36ኛ ሳምንት ጥናት(8፡1-11)

  ሆኖም ግን ተመልሰው መጡ፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ቂመኛ አይደለምና ዳግመኛ አስተማራቸው፡፡ “እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ፤ የሚከተለኝ የሕይወት ብርሃን ይሆንለታል እንጂ በጨለማ አይመላለስም” ብሎ ተናገራቸው /ቁ.12/፡፡ እንዴት ያለ ፍቅር ነው? እንደምን ያለ መውደድ ነው? ፍቁራን ሆይ! የጌታን ንግግር ታስተውሉታላችሁን? እንዲህ ማለቱ ነበር፡-“ፈሪሳውያን ሆይ! እናንተ በመጻሕፍተ ኦሪት የዘለዓለም ሕይወት እንዳለችሁ ይመስላችኋል፤ እነርሱንም ትመረምራላችሁ፡፡ እነርሱ ግን ስለ እኔ የሚመሰክሩ ናቸው /ዮሐ.5፡39/፡፡ እንግዲያውስ ወደ እኔ ኑ እንጂ በዚያ የምትቀሩ አትሁኑ! ዳዊት ‘የሕይወት ምንጭ ከአንተ ዘንድ ነውና በብርሃንህ ብርሃንን እናያለን’ እንዳለ /መዝ.36፡6/ የሕይወት ምንጭ እኔ ነኝና ወደ እኔ ቅረቡ እንጂ በጨለማ የምትቆዩ አትሁኑ፡፡ እውነተኛው ብርሃን እኔ ነኝና ወደ ብርሃን (ወደ እኔ) ኑ! በጨለማ ላለ ሰው ብርሃን ያስፈልጓል፡፡ የተጠማ ሰውም የሚያረካ መጠጥ ያስፈልጓል፡፡ እንግዲያውስ የእነዚህ ምንጫቸው እኔ ነኝና ታገኝዋቸው ዘንድ ወደ እኔ ቅረቡ (በእኔ እመኑ)፡፡ ከእናንተ መካከል አንዱ በሌሊት ውኃ ቢጠማው ተነሥቶ ኩራዝን የማያበራ ማን ነው? ኩራዙንም ተጠቅሞ ውኃ ቀድቶ የሚጠጣ አይደለምን? እንግዲያውስ እናንተም በብርሃኔ ብርሃን የሆንኩትን እኔን ያዙና ዳግመኛ ጽምዓ ነፍሰን የማያስጠማ የሕይወትን ውኃ ጠጡ፡፡ ልጆቼ ሆይ! በጨለማ (በድንቁርና) መኖርን ስለምን ትመርጣላችሁ? እናንተን እንዲሁ አፍቅሬ አማናዊው ብርሃን የምሆን እኔ ወደ እናንተ ስመጣ ስለምን ዐይነ ልቡናችሁን በመዝጋት እኔን ከማየት ትከለከላላችሁ? አባቶቻችሁ ከምድረ ግብጽ ለመውጣት ፊት ለፊት የሚመራቸውን ዓምደ ብርሃንን ተከትለው ከባርነት የወጡ አይደሉምን? /ዘጸ.13፡21/ እንግዲያውስ እናንተም ወደ እውነተኛው ሀገራችሁ (ወደ ገነት መንግሥተ ሰማያት) ለመግባት ብርሃን እኔን ተከተሉ፡፡ እኔ የፍልስጥኤም ወይም የገሊላ ወይም ደግሞ የይሁዳ ብቻ ሳልሆን የዓለም ሁሉ ብርሃን ነኝ፤ የሚከተለኝ(የሚያምንብኝ) ቢኖር የሕይወት ብርሃን ይሆንለታል፡፡ ክብርን፣ ዕውቀትን፣ መንግሥተ ሰማያትን ያገኛል እንጂ በሐሳር፣ በጨለማ ፣ በገሃነም አይመላለስም፡፡ የሚከተለኝ ቢኖር በሴሰኛይቱ ሴት እንዳደረጋችሁት ሳይሆን በራሱ ኃጢአት ላይ ስለሚፈርድ በእኔ አምኖ ይኖራል፡፡ ወደ ክሕደት፣ ወደ ገሃነም፣ በሌሎች ላይ ወደ መፍረድ፣ ወደ ክፉ ነገር አይሄድም፡፡ የሕይወትን ውኃ ክብረ መንግሥተ ሰማያትን ታገኛል፡፡ ስለዚህ በእኔ እመኑና ከስሕተት ከክሕደት ውጡ” /St. Cyril of Alexandria on the Gospel of John, 5:2/፡፡ 

   ፈሪሳውያን ግን ይህን ፍቅር ከመረዳት ራቁ፡፡ መድኅን የሆነው ስሙ ከፍ ከፍ ይበልና አፍቃሪያቸውን እንደ “ዕሩቅ ብእሲ” አይተዉት “የሌለውን አምላክነት” ለራሱ የወሰደ መሰላቸው፡፡ ስለዚህ፡- “አንተ ስለ ራስህ ትመሰክራለህን?” ራስህን የምታመሰግን፣ ራስህንም የምታደንቅ ከሆነማ… አሉት፡፡ ሐሰት የባሕርይው ያይደለ አምላክ “ምስክርነትህ (የምትናገረው ሁሉ) እውነት አይደለም” አሉት /ቁ.13/።  የሚደንቀው ግን

Wednesday, September 12, 2012

ዜና ሐዋርያት


 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
   መንደርደርያ ይሆነን ዘንድ እስከ አሁን ባቀረብናቸው ሁለት ክፍሎች (እነዚያን ለማንበብ ይህን ይጫኑ http://mekrez.blogspot.com/2012/08/blog-post_7538.html) ክርስቲያኖች ለባሴ ክርስቶስ (ክርስቶስን የለበሱ) ዘላለማዊ ሕይወትን የያዙ ማለት እንደሆኑና ቅዱሳን ደግሞ ዘላለማዊ በሆነ በክርስቶስ ከፍተኛ የቅድስና ደረጃ ላይ የደረሱ፣ ሞት የማይሠለጥንባቸው ፍጹማን ክርስቲያኖች፣ ሁለንተናዊ ሕይወታቸው በክርስቶስ የሆነ እንደሆኑ ተመልክተናል። ከዚህ በተጨማሪ እኛም እንደ እነርሱ እውነተኞች የተግባር ክርስቲያኖች ለመሆንና በክርስቶስ በሕይወት ለመኖር የቅዱሳንን ሕይወትና ታሪክ ማጥናትና እነርሱን ለመምሰል መጣጣር መተኪያ የሌለው ጉዳይ እንደሆነ ተመልክተናል። እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በሚቀጥሉት ጊዜያት ከቅዱሳን ሐዋርያት ጀምሮ በየዘመናቱ የተነሡ ቅዱሳንን ታሪክ እናቀርባለን። ለዛሬ የቅዱሳን ሐዋርያትን ታሪክ መግቢያ እነሆ!
  ነቢያትን ትንቢት ያናገረ አምላክ፣ ወልደ አብ ወልደ ማርያም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም ሰው ሆኖ ከኃጢአት በስተቀር የሰውን ሥራ በመሥራት አደገ፡፡ በሠላሳ ዓመቱም በባርያው በዮሐንስ እጅ ተጠመቀ፡፡ በገዳመ ቆሮንቶስ መዓልትና ሌሊት ጾመ፤ ተራበ፤ ተጠማ፤ በዲያብሎስ ተፈተነ፡፡ ከዚህም በኋላ ወንጌለ መንግሥቱን ማስተማር ጀመረ፡፡ በሚያስተምርበት ወቅትም ለተለያዩ ዓላማዎች ብዙ ሕዝብ ( ገበያ ያህል) ይከተሉት ነበር። ግማሹይሤኒ ላህዩ እምውሉደ ዕጓለ እመሕያው- መልኩ ከሰው ልጆች ሁሉ ያምራልእንዲል /መዝ.452/ መልኩን ለማየት፤ ግማሹ በአምስት እንጀራና በሁለት ዓሣ አምስት ሺህ ሕዝብ ሲመግብ አይተው /ማቴ. 1416/ ሕብስት አበርክቶ ይመግበናል ብለው፤ ግማሹ ልዩ ልዩ ደዌ ያደረባቸውን ሰዎች በተአምራት ይፈውስ ነበርና ከበሽታቸው ለመፈወስ ይከተሉት ነበር /ማቴ.423/ ጌታችንም ከዚህ ሁሉ ሕዝብ መካከል መቶ ሃያ ቤተሰቦችን መረጠ። ምክንያቱ ደግሞ እነርሱ ከዋለበት እየዋሉ ካደረበት እያደሩ ትምህርቱን ሰምተው ተአምራቱን አይተው በሚገባ የሚከታተሉቀለምተማሪዎች ስለነበሩ ነው። ከእነዚህም ውስጥ አስቀድመው የተመረጡት ቅዱሳን ሐዋርያት ሲሆኑ (እርሱም ጸጋን ሰጠ፤ ከቤተሰቦቹም ሐዋርያትን፣ ከእነርሱም ነብያትንና የወንጌል ሰባኪዎችን ጠባቂዎችንና መምህራንን ሾመ። ኤፌ. ፬፣፲፬) በኋላ ፸፪ቱ አርድእት (ከዚህም በኋላ ሌሎች ሰባ ሰዎችን መረጠ ሉቃ. ፲፣፩) ቀጥሎ ደግሞ ፴፮ቱ ቅዱሳት አንስት ተመርጠዋል። ፲፪ + ፸፪ + ፴፮ = ፻፳ መቶ ሃያ ቤተሰብ የሚባሉ እነዚህ ናቸው።
  ሐዋርያ የሚለው ቃልሖረከሚለው የግዕዝ ግስ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙምለማስተማር የተላከማለት ነው፡፡ የአሥራ ሁለቱም ሐዋርያት ስም፡- ጴጥሮስ፣ እንድርያስ፣ ያዕቆብ፣ ዮሐንስ፣ ፊሊጶስ፣ በርተለሜዎስ፣ ቶማስ፣ ማቴዎስ፣ ያዕቆብ ወልድ እልፍዮስ፣ ታዴዎስ የተባለ ልብድዮስ፣ ስምዖን ቀኖናዊ እንዲሁም የአስቆሮቱ ይሁዳ ናቸው /ማቴ.101-4/፡፡    አባቶቻችን ቅዱሳን ሐዋርያት ምንም እንኳን ትውልዳቸው ከ፲፪ቱ ነገደ እስራኤል ቢሆንም የተመረጡት ግን በጌትነት ከሚኖሩ ከመሳፍንትና ከመኳንንት ወይም ከባለጸጎች ወገን ሳይሆን ከድሆች (ብዙዎች ሐዋርያት ዓሣ አጥማጆች ነበሩ) ካልተማሩትና በአጠቃላይ በኅብረተሰቡ ዘንድ ዝቅተኛ ስፍራ ከሚሰጣቸው ወገኖች ነበሩ። የዚህም ምክንያት ሐዋርያውወንድሞቻችን! እንግዲህ እንዴት እንደተጠራችሁ እዩ፤ በሥጋ እጅግ ብዙዎች ዐዋቂዎች አይደላችሁምና፤ ብዙዎች ኃያላንም አይደላችሁምና፤ በዘመድም ብዙዎች ደጋጎች አይደላችሁምና። ነገር ግን እግዚአብሔር ጥበበኞችን ሊያሳፍር የዚህን ዓለም ሰነፎች መረጠ፤ ኃይለኞችንም ያሳፍር ዘንድ እግዚአብሔር የዚህን ዓለም ደካሞች መረጠ። አለን የሚሉትንም ያሳፍር ዘንድ ዘመድ የሌላቸውን የተናቁትን፤ ከቁጥርም ያልገቡትን እግዚአብሔር መረጠብሎ እንደተናገረው ሰው በጥበቡና በኃይሉ በትውልዱም በእግዚአብሔር ፊት መመካት እንደማይገባው በተግባር ለማስገንዘብ ነው (፩ቆሮ. ፩፣፳፮- ፍጻሜ)
  ጌታችን እነዚህን መርጦ ሐዋርያት ብሎ ከሰየማቸው በኋላ (ከዕርገት በኋላ እርሱን ተክተው ሐዋርያት መደበኞች ሆነው አርድእት ደግሞ ሐዋርያትን እየረዱ የሚያስተምሩ ናቸውና!) ለጊዜው በምድረ እስራኤል ብቻ እንዲያስተምሩ ላካቸው፡፡ የዚህ ዓለም ወታደር ወደ ጦር ሜዳ ሲሄድ በቂ ስንቅና ትጥቅ እንደሚሰጠው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ለቅዱሳን ሐዋርያትበአሕዛብ መንገድ አትሂዱ ወደ ሳምራውያን ከተማም አትግቡ።  ነገር ግን ከእስራኤል ወገን ወደ ጠፉት በጎች ሂዱ። ሄዳችሁም መንግሥተ ሰማያት ቀርባለች እያላችሁ አስተምሩ። ድውያንን ፈውሱ፤ ሙታንንም አንሡ፤ ለምጻሞችንም አንጹ፤ አጋንንትንም አውጡ፤ ያለዋጋ የተቀበላችሁትን ያለዋጋ ስጡብሎ ድውይ የሚፈውሱበት፣ ሙት የሚያስነሡበት፣ ጋኔን የሚያወጡበት፣ ለምጽ የሚያነጹበት ሙሉ ትጥቅ ሰጣቸው፤መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችእያሉ እንዲያስተምሩም ላካቸው /ማቴ. ፲፣፭ - /  በተመሳሳይ ሁኔታ አርድእቱንም እንደላካቸው በሌላ ቦታ ተጽፎ እናገኛለን (ሉቃ. )
 ከዚህም በተጨማሪእነሆ እንደበጎች በተኩላዎች መካከል እልካችኋለሁ፤ እንግዲህ እንደእባብ ብልሆች እንድርግብም የዋሆች ሁኑ። ከክፉዎች ሰዎች ተጠበቁ፤ ወደ አደባባዮች አሳልፈው ይሰጧችኋልና፤ በምኩራቦቻቸውም ይገርፏችኋልናእያለ ወደፊት በስሙ ሲያስተምሩ ዓለም እንደሚጠላቸውና መከራ እንደሚያመጣባቸው፤ ይህንንም መከራ እንዴት እንደሚያሸንፉት ከነመፍትሔው ነገራቸው /ማቴ. ፲፣፲፯ ዮሐ. ፲፭፣፲፰- ፳፭/
  ከዚህ በኋላ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፅንስ የጀመረውን የማዳን ሥራ በሞቱ በቀራንዮ ፈጸመው፡፡ ዓለምን አድኖም መዓልትና ሌሊት በከርሠ መቃብር አድሮ ሙስና መቃብርን አጥፍቶ ተነሣ። ከትንሣኤው በኋላ ለሐዋርያት በጉባኤም በተናጠልም (ለአንዱ ለሁለቱ) እየተገለጸ ቀን አስተማራቸው። በ፵ኛው ቀን ኃይል፣ ጽንዕ የሚሆናቸው መንፈስ ቅዱስን እንደሚልክላቸው ተስፋ ሰጥቷቸው እስካሁን ያዩትንና የሰሙትን እውነት ለዓለም እንዲመሰክሩ አዝዟቸው ዐረገ። ባረገ በ፲ኛው ቀንም የተናገረውን የማያስቀር ጌታሁሉም መንፈስ ቅዱስን ተሞሉ፤ ይናገሩ ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እንዳደላቸው መጠንም እየራሳቸው በሀገሩ ሁሉ ቋንቋ ይናገሩ ጀመሩእንዲል ጰራቅሊጦስን (መንፈስ ቅዱስን) ሰደደላቸው /ሐዋ. / ጰራቅሊጦስ ማለት በፅርእ ቋንቋ የሚያጽናና የሚያስደስት ማለት ነው፡፡
 አባቶቻችን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ ፸፪ ቋንቋ ተገልጦላቸው በዕውቀት ጐለመሱ፤ ከብልየት ታደሱ፤ ፈሪዎች የነበሩ መከራ ሥጋን የማይፈሩ ጥቡዐን ሆኑ። መዲናቸው ኢየሩሳሌምን በኅብረት ካስተማሩ በኋላ ሑሩ ወመሀሩ- ሂዱና አስተምሩያላቸውን ቃል በመጠበቅ ዓለምን በዕጣ ተከፋፍለው አርድእት ደግሞ ሐዋርያትን ተከትለውአምላክ ከሰማያት ወረደ፤ በድንግልና ተፀንሶ በድንግልና ተወለደ፤ የምሥራችን አስተማረ፤ በአይሁድ እጅ ተገፈፈ ተገረፈ፤ በመስቀል ተሰቀለ፤ ሞተ፤ ተቀበረ፤ መቃብር ክፈቱልኝ መግነዝ ፍቱልኝ ሳይል በኃይሉና በሥልጣኑ በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ፤ በክብር በምስጋና ወደ ሰማይ ዐረገ፤ ዳግመኛም ለፍርድ ይመጣልብለው ወንጌልን ለዓለም ሁሉ ሰበኩ፤ ለቤተ ክርስቲያን ሕግ አወጡ፤ ሥርዓት ደነገጉ፡፡ ነቢዩ ዳዊትውስተ ኵሉ ምድር ወጽአ ነገሮሙ ወእስከ አጽናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙትርጉሙምድምፃቸው ወደ ምድር ሁሉ ቃላቸውም እስከ ዓለም ዳርቻ ወጣብሎ የተናገረው ትንቢት ደረሰ፤ ተፈጸመ (መዝ. ፲፰ )
  ጌታችን በተራራው ስብከቱ ላይ ሲያስተምራቸውእናንተ የምድር ጨው፣ የዓለም ብርሃንና የተራራ ላይ መንደር ናችሁብሏቸው ነበርና በትምህርታቸው በትሩፋታቸው አልጫውን ዓለም በሃይማኖትና በአምልኮተ እግዚአብሔር አጣፈጡት። በኃጢአት ጨለማ ውስጥ የነበረውን የሰው ልጅ በንጽሕናና በቅድስና ወንጌል ብርሃን አበሩት። በድንቁርና ዋሻ ተሰውሮ የነበረውን የአሕዛብን ልብ በዕውቀት ተራራ ላይ አውጥተው ለዓለም ሁሉ እንዲገለጥና እንዲታይ አደረጉት። ይህን ሁሉ ሲያደርጉ የሐዋርያዊ አገልግሎታቸው ዋነኛ መሣሪያዎች ጌታቸውና መምህራቸው እንዳዘዛቸው ጥበብ፣ ትዕግሥት፣ ፍቅርና የዋህነት ነበሩ። በዚህ ሁኔታ የተመረጡለትን ታላቅ አምላካዊ ዓላማ አሳኩ፡፡ በኋላም የጌታቸውን አርአያ ተከትለው ያላመኑ አይሁድና አሕዛብ እኩሉን በገመድ እያነቁ፣ እኩሉንም በደንጊያ እየወገሩ፣ እኩሉንም በሰይፍ እየመቱ በልዩ ልዩ ዓይነት ስቃይ  እያሰቃዩ ገደልዋቸው፡፡ ሐዋርያትም ቁልቁል ተሰቅለው፣ በሰይፍ ተከልለው፣ እንደ በግ ተገፈው፣ በእሳት ተጠብሰው በድንጋይ ተወግረው ሰማዕትነትን ተቀብለው የመከራ ወንዝ የሆነ ይህን ዓለም ተሻገሩ፡፡ ሰውን ከሰው አላገናኝ ያለውን የቋንቋ፣ የጐሣ፣ የቅንዓትና የምቀኝነት ወንዝ ተሻግሮ እምነት፣ ተስፋ፣ ፍቅር ከሚገኝበት ከተማ የሚያደርሰውን ድልድይ ሠርተው ተልእኮአቸውን ጨረሱ፡፡የምሄድበት ጊዜዬ (ለሞት ዕድሜዬ) ደርሷል፡፡ መልካሙን ገድል ተጋድያለሁ፤ ሩጫውን ጨርሻለሁ፤ ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ፤ ወደ ፊት የጽድቅ አክሊል ተዘጋጅቶልኛል፤ ይህንም ጻድቅ ፈራጅ የሆነው ጌታ ያን ቀን ለእኔ ያስረክባል፤ ደግሞም መገለጡን ለሚወዱት ሁሉ እንጂ ለእኔ ብቻ አይደለምበማለት መስክረው አለፉ /፪ጢሞ.፬፡፮-/፡፡
  ሐዋርያት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በአካል በዓይናቸው ያዩ፣ ቃሉን ከእግሩ ሥር ቁጭ ብለው የተማሩና በጆሮዎቻቸው የሰሙ፣ በእጃቸውም የዳሰሱት በአጠቃላይ ዓመት ከ፫ወር ሲያስተምር ከዋለበት እየዋሉ ካደረበት እያደሩ አብረውት የነበሩ፣ በኋላም ክርስቶስ በደሙ የመሠረታትን ቤተ ክርስቲያን አጥንታቸውን ከስክሰው፣ ደማቸውን አፍሰው፣ ሥጋቸውን ቆርሰው ስለገነቧት ቅድስት ቤተክርስቲያን ከፍተኛና ለየት ያለ ቦታ ትሰጣቸዋለች። ለመታሰቢያቸውም የቤተ ክርስቲያን ጣራ ፲፪ ዐምድ (ምሰሶ) እንዲኖረው ሊቃውንት ወስነዋል፡፡ ስለዚህ ሐዋርያት ከጌታችን ያዩትንና የሰሙትን ወንጌል ያስተላለፉ የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ስለሆኑ የቤተክርስቲያን መሠረቶች ናቸው። ከእነርሱ አስተምህሮና ትውፊት የወጣች ቤተክርስቲያን ቤተክርስቲያን ልትባል አትችልም። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስምእናንተ ግን የእኛን ፍለጋ ተከተሉ፤ እናንተስ እኛም ብንሆን ወይም መልአክ ከሰማይ ወርዶ እኛ ካስተማርናችሁ ወንጌል ሌላ ቢሰብክላችሁ ውጉዝ ይሁን። አስቀድሜ እንዳልሁ አሁንም ደግሜ እላለሁ ካስተማርናችሁ ሌላ ትምህርት ያስተማራችሁ ቢኖር ውጉዝ ይሁንበማለት ከሐዋርያት ትምህርት የሚወጣውን አስቀድሞ አውግዟል (ገላ. ፩፣ -)፡፡
   እግዚአብሔር ቢፈቅድና ብንኖር በቀጣይ ጊዜ የእያንዳንዱን ሐዋርያ ታሪክና ሐዋርያዊ ጉዞ በተከታታይ ለማቅረብ እንሞክራለን። ለዚህም የእግዚአብሔር ቸርነት፣ የእመ ብርሃን አማላጅነት፣ የቅዱሳን ሐዋርያት በረከታቸውና ረድኤታቸው አይለየን አሜን!!
         






FeedBurner FeedCount