Friday, July 31, 2015

የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም ገዳም መምህራንና ቀሳውስት ማሠልጠኛ መንፈሳዊ ት/ቤት ትናንት፣ ዛሬና ነገ



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐምሌ 24 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኘው የታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም ገዳም መምህራንና ቀሳውስት ማሠልጠኛ ተቋም ከተመሠረተ ከ82 ዓመታት በላይ ኾኖታል፡፡ በእነዚህ አገልግሎት ዘመናቱም በርካታ ታላላቅ የሃይማኖት አባቶች ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቤተክርስቲያን ሊቃውንት፣ አባቶች መምህራንና ካህናትን አፍርቷል፡፡ ማሠልጠኛው ጥንታዊው የሀገራችን ቋንቋና ፊደል ግእዝና ትምህርቱ ተጠብቆ እንዲቆይ ለትውልድም እንዲተላለፍ በማድረግ በኩል ታላቅ ድርሻ አለው፡፡ የቤተክርስቲያን አባቶችና ምእመናን ኹሉ የቤተ ክርስቲያን አለኝታና ቅርስ መኾኑን በኩራት የሚናገሩለት ተቋም ነው፡፡
ይኼው ማሠልጠኛ በረጅም ጊዜ አገልግሎት ለቤተክርስቲያንም ኾነ ለሀገር ከፍተኛ አገልግሎትና ጥቅም የሰጠ ነው፡፡ በዚህም መሠረት የዚህን ት/ቤት ትናንት የነበረውን ገጽታ ዛሬ ያለበትንና ወደፊት የሚጠበቅበትን በዚህች አነስተኛ ጽሑፍ እንዳስሳለን፡፡

Sunday, July 26, 2015

....... ሰላም ገብርኤል.......



በልዑል ገ/እግዚአብሔር
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐምሌ 19 ቀን 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!


ሰላምታየሰላማዊ አካል ስጦታ
................
በጎነት አክብሮት ምሣሌው
የታላቅነት ትርጓሜ የሰሪውን ማንነት
...........
አንድ የመሆን ምስጢር ሲለው

ሰላም...!
ነገረ ፈጅ የእስራኤል ባለጠጋ
.........
መመረቅ መርገም ቢችልበት
ባላቅ ደስ ሊለው...
የፀጋውን ስጦታ ቅዱሱን ሊረግምበት
..............
አህያውን ይዞ ተጓዘበት

Tuesday, July 21, 2015

ትምህርተ ሃይማኖት (ክፍል ዐሥራ ሦስት)



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐምሌ 14 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
የእሑድ ሰዓተ መዓልት ፍጥረታት
ሀ) በአንደኛው ሰዓተ መዓልት፡- እግዚአብሔር በዚህ ጊዜ “ብርሃን ይኹን” ብሎ ብርሃንን በስተምሥራቅ በኩል ፈጠረ፡፡ ከዚህም በኋላ መንፈስ ቅዱስ ዓለምን እንደ እንቁላል በክንፉ ዕቅፍ አድርጐ ለመላእክት ታያቸው፡፡ መላእክቱንም እንዲህ ሲል ጠየቃቸው፡- “ይህ ኹሉ ሰማይ የእኔ ነው፡፡ ታዲያ ከቤቴ ማን አገባችሁ? ከወዴትስ መጣችሁ?” መላእከቱም፡- “አቤቱ ከግሩማን በላይ ያለህ ግሩም አንተ ነህ፡፡ በዚህን ያህል ድንጋፄ ያራድከን ያንቀጠቀጥከን እናውቅህ ዘንድ አንተ ማን ነህ?” አሉት፡፡ መንፈስ ቅዱስም “ሰማይን፣ ምድርን፣ እናንተንም ለፈጠረ ለአብ ሕይወቱ ነኝ” አላቸው /ኄኖክ.13፡21-22/፡፡ መላእክትም “አቤቱ ጌታችን የፈጠረንንስ፣ ያመጣንንስ ከቤትህስ ያገባንን አንተ ታውቃለህ እንጂ እኛ ምን እናውቃለን” ብለው ፈጣሪነቱ የባሕርዩ እንደኾነ አመኑለት፤ መሰከሩለት፡፡
ሳጥናኤልም መላእክትና መንፈስ ቅዱስ ሲነጋገሩ ቢሰማ ደነገጠ፤ ሐሳቡ ከንቱ ስለኾነበትም አፈረ /ኢሳ.14፡12-16/፡፡ ወዲያውም ያ በምሥራቅ የተፈጠረ ብርሃን እንደ ምንጭ እየፈሰሰ እንደ ጐርፍ እየጐረፈ ደርሶ አጥለቀለቃቸው፤ ዋጣቸው፡፡ ብርሃኑ የመጣው እግዚአብሔር ከአራቱ ባሕርያተ ሥጋ አንዲቱ ማለትም እሳቲቱን ብርሃን ውለጂ ብሎ ሲያዝዛት ነው፡፡ ከዚያም በኋላ ብርሃኑን መዓልት ብሎ ጠራው፡፡ ከዚያ በፊት ተፈጥሮ የነበረው ጨለማውን ደግሞ ሌሊት ብሎ ጠራው /ዘፍ.1፡5-6/፡፡ በዚሁም የብርሃንን ሥራና የጨለማ ሥራ ለይተን እንኖር ዘንድ ሲያስተምረን ነው፡፡

Monday, July 13, 2015

ትምህርተ ሃይማኖት (ክፍል ዐሥራ ኹለት)



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐምሌ 6 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ክሕደተ ሰይጣን
ሰይጣን በዕብራይስጥ ሲኾን ዲያብሎስ ደግሞ በግሪክኛ ነው፡፡ ትርጓሜውም አሰናካይ፣ ባለ ጋራ፣ ወደረኛ፣ ጠላት፣ ከሳሽ፣ ተቃዋሚ ማለት ነው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በተቃወመው ጊዜ፡- “ወደኋላዬ ሒድ አንተ ሰይጣን፤ … ዕንቅፋት ኾነህብኛል” መባሉም ስለዚሁ ነው /ማቴ.16፡23/፡፡
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥም ከ40 በላይ በኾኑ የተለያዩ ስሞች ተገልጾ እናገኟለን፡፡ ጥቂቶቹን ለመጥቀስ ያህልም፡-
·         የቀድሞ ክብሩን ለመግለጽ - የአጥቢያ ኮከብ /ኢሳ.14፡12/፤
·         ምእመናንን እንዲሁ በሐሰት ይከሳልና- ከሳሽ /ራእ.12፡10/፤
·         ገዳይነቱንና ኃይለኝነቱን ለመግለጽ - ዘንዶ /ራእ.12፡3/፤
·         ክፋት እንዲበዛ የሚያደርግ ነውና - ክፉው /ማቴ.13፡19/፤
·         ከዋነኞቹ ግብሮቹ ለመግለጽ - ፈታኙ /ማቴ.4፡3/፤
·         የርኩሰት ጌታዋ ነውና - ብዔል ዘቡል /ማቴ.12፡24-27/፤
·         ወዘተርፈ
ሰይጣን እግዚአብሔርንና የእግዚአብሔር የኾኑትን ተቃውሞ የወደቀው የመጀመሪያው መልአክ ነው፡፡ ምንም እንኳን መልካም የኾነውን ኹሉ እየተቃወመ የራሱን መንግሥት ሊያቆም የሚጥር ቢኾንም ከእግዚአብሔር ጋር የተካከለ መንግሥት (መለኮታዊ ባሕርይ) የለውም፤ መለኮታዊ ባሕርይ የእግዚአብሔር ገንዘብ ብቻ ነውና፡፡

Thursday, July 9, 2015

መቅረዝ ዘተዋሕዶ : ብርሃናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ

መቅረዝ ዘተዋሕዶ : ብርሃናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ: (መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐምሌ ፭ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!   በዛሬው ዕለት የምናከብረው በዓል ኹለቱም ታላላቅ ሐዋርያት በሰማዕትነት ያረፉበትን በዓል ...

Sunday, July 5, 2015

ደጃፉንም ለማግኘት ሲፈልጉ ደከሙ /ዘፍ.19፡11/


በዲ/ን ዶ/ር ቴዎድሮስ በለጠ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሰኔ 28 ቀን 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
"ወደላይ አቅንተን እንለምን ያን ጊዜ የመለኮትን ነገር ከሚናገሩ መጻሕፍት እውቀት ይገለጽልናል" ይህን ቃል ለቅዱስ ጳውሎስ የመንፈስ ልጅ ለጢሞቴዎስ የላከው በአርዮስፋጎስ (መካነ-ጥበብ) የሚያስተምር የአቴናው ኤጲስ ቆጶስና ለቅዱሳን ሐዋርያት ተከታይ የሆነ ሊቁ ድዮናስዮስ ነው::(ሃይማኖተ አበው ም.10 ቁ.2)
ለዛሬ ያለውን ትምህርታችንን ከላይ ያነሣነውን መሪ ቃል መነሻ በማድረግ የምናይ ሲሆን ለዚሁም በቸርነቱ ብዛት እውቀትን ጥበብን ምስጢርንና ማስተዋልን ለሰው ልጆች ሁሉ የሚገልጥ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ የራቀውን አቅርቦ የረቀቀውን አጉልቶ የተሰወረውን ገልጦና የተከደነውን ከፍቶ የቅዱሳት መጻሕፍትን ጥልቅ ሃሳብ እንድንረዳ ይርዳን!

Thursday, July 2, 2015

የንስሐ አባቴ ኃጢአቴን ቀለል አድርገው ስለሚነግሩኝ ንስሐ ለመግባት እቸገራለሁ፡፡ ምን ላድርግ?



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሰኔ 25 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ውድ መቅረዛውያን እንዴት አላችሁ? ዛሬም ከአንባብያን ከተላኩልኝ ጥያቄዎች መካከል አንዱን መርጬ በአበው ካህናት የተሰጠውን ምላሽ ይዤላችሁ ቀርቢያለሁ፡፡ ዛሬም መልሱን የሚሰጡን በምሥራቀ ፀሐይ ቀበና መድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን ሰባኬ ወንጌል እንዲሁም መጋቤ አእላፍ ቀሲስ ፋሲል ታደሰ ናቸው፡፡ ለአባታችን ተናጋሪ አንደበት ለእኛም ሰሚ እዝነ ልቡና ያድለን፡፡ አሜን!!!
ጥያቄ፡-  “ውድ የመቅረዞች አዘጋጆች! እንዴት አላችሁ? የመቅረዝ ዘተዋሕዶ አንባቢ ነኝ፡፡ ከምእመናን የምታስተናግዱት ጥያቄ በጣም ጥሩ ነው፡፡ እኔም ከንስሐ አባት ጋር የተያያዘ ጥያቄ አለኝ፡፡ ለካህናት እንዲህ አደረግኩ ብዬ ስናገር፡- ‘ምንም ችግር የለውም፡፡ ይህቺ’ማ ምን አላት?’ እያሉ በተደጋጋሚ ስለሚነግሩኝ ሌላውን ለመናገር ቸገረኝ፡፡ ምን ላድርግ?”
አንዳርግ ነኝ ከቺካጎ

Monday, June 22, 2015

ሒዱ እንጂ ተቀመጡ አልተባልንም (ክፍል ኹለት)



በዲ/ን ዳንኤል ክብረት
(መዝረቅ ዘተዋሕዶ፣ ሰኔ 16 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ኹለተኛው በይሁዳ ነው!
ይሁዳ የኢየሩሳሌም አውራጃው ነው፡፡ የይሁዳ አውራጃ ዋና ከተማም ኢየሩሳሌም ነች፡፡ ከኢየሩሳሌም ይሁዳ ይከፋል፤ ከሰማርያ ግን ይሻላል፡፡ ምክንያቱም ኢየሩሳሌም ዋና ከተማዋ ነች፣ ጌታም የተወለደው በይሁዳ አውራጃ በቤተ ልሔም ነው፡፡ የተሰቀለው፣ የሞተው፣ የተቀበረው፣ ያረገው፣ መንፈስ ቅዱስን ለሐዋርያት የላከው በኢየሩሳሌም ከተማ ነው፡፡ ስለዚህ የኢየሩሳሌም ነገር በይሁዳ አውራጃ የተሻለ ይወራል፤ ይነገራል፡፡ የሚያውቁት ዘመድ ይኖራል፡፡ የሐዋርያትና የይሁዳ ቋንቋ ተመሳሳይ ነው፡፡ የይሁዳ ባሕልና የኢየሩሳሌም ባሕል ተመሳሳይ ነው፡፡ ከሰማርያ ቢሻልም ከኢየሩሳሌም ግን ይከፋል፡፡

Tuesday, June 16, 2015

ሒዱ እንጂ ተቀመጡ አልተባልንም (ክፍል አንድ)



በዲ/ን ዳንኤል ክብረት
      (መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሰኔ 9 ቀን 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
     ውድ የመቅረዝ አንባብያን! እንዴት አላችሁ? ይህ ጽሑፍ ዲ/ን ዳንኤል ክብረት ማኅበረ ቅዱሳን ሰኔ 7 ቀን 2007 ዓ.ም. ወደ ቡኢ ደብረ ሰላም በዓለ ወልድ ቤተ ክርስቲያን ባዘጋጀው የበእንተ ወንጌል መርሐ ግብር ላይ ያስተማረው ትምህርት ነው፡፡ ስብከቱ አንድ ሰዓት ከዐሥር ደቂቃ የሚፈጅ ስለኾነ ወደ ጽሑፍ ሲቀየር ትንሽ በዛ ይላል፡፡ በመኾኑም በኹለት ክፍል እንዳቀርበው ተገድጃለሁ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ዲ/ን ዳንኤል ሲሰብክም የሚያነብ ስለሚመስል ብዙ የሚደጋገሙ ዐረፍተ ነገሮችን ስለሌሉበት፥ ያስተካከልኩት ነገር ቢኖር በጉባኤው ላልነበረ ሰው የማይረዱ ጥቃቅን ስንኞችን ብቻ ነው፡፡ ስለ ኹሉም መልካም መልካም ንባብ ይኹንላችሁ!!!

Thursday, June 11, 2015

መልከኞቹ



በደቀ መዝሙር ተስፋሁን ነጋሽ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሰኔ 4 ቀን 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
አንዲት ባለጠጋ እናት አሉ፡፡ ታዲያ ቀደም ሲል ካከበርናቸው ዐበይት በዓላተ እግዚእ መካከል አንዱ የሆነውን በዓለ ጰራቅሊጦስ አብሬአቸው እንዳሳልፍ በክብር ጋብዘውኝ ከቤታቸው ተገኘሁ፡፡ እኒያ እናት ሦስት ልጆች ያላቸው ሲሆን የልጆቹ ውበት ልዩ ነው፡፡ እንዲያውም አንድ ወዳጄ የልጆቹን መልክ ዓይቶ ‹‹በሥላሴ አምሳል የተፈጠሩትስ እኒህ ልጆች ናቸው›› ሲለኝ በፈገግታ ማለፌን አልዘነጋውም፡፡ አንዱን አይታችሁ ወደ ሌላኛው ስትዞሩ የባሰ እንጂ ያነሰ ቁንጅና አታዩም፡፡ በመሆኑም ወደዚያ ቤት የገቡ እንግዶች ሁሉ ስለ ልጆቻቸው ቁንጅና ሳይናገሩ አይወጡም፡፡ ስለ ትልቁ ልጃቸው ግርማ ሞገስ፣ ስለ ተከታይዋ ሸንቃጣነት፣ ስለ ትንሹ ልጃቸው ቅላት አንዱ ከሌላው አፍ እየነጠቀ የልቡን አድናቆት ይገልጣል፡፡ እናት ስለ ልጆቻቸው የሚባለውን ሁሉ ከሰሙ በኋላ ግን ‹‹ልክ ናችሁ ልጆቼ መልክኞች ናቸው፤ ግን ኃይለኞች አይደሉም›› ይላሉ፡፡ ይህ ንግግራቸው እኔን ግራ ስላጋባኝ ‹‹ምን ማለትዎ ነው? አሁን እነዚህ ልጆች ምን ይወጣላቸዋል?›› በሚል የአድናቂነት ወግ ጠየቅኋቸው፡፡ እርሳቸውም ‹‹መልሱ ያለው ሁለተኛ ጢሞቴዎስ ላይ ነው›› አሉኝና ‹‹የአምልኮት መልክ አላቸው ኃይሉን ግን ክደዋል፤ ከእነዚህ ደግሞ ራቅ›› የሚለውን ቅዱስ ቃል አነበቡልኝ፡፡ /2ኛ ጢሞ. 3፤5/

Monday, June 8, 2015

ትምህርተ ሃይማኖት (ክፍል ዐሥራ አንድ)

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሰኔ 2 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
የእሑድ ዕለት ፍጥረታት
የእሑድ ሰዓተ ሌሊት ፍጥረታት
እሑድ ማለት የዕለታት መጀመሪያ ማለት ሲኾን ይኸውም እግዚአብሔር ፍጥረቱን የፈጠረበት የመጀመሪያው ቀን ነው፡፡ በዚህ ዕለት ስምንት ፍጥረታት የተፈጠሩ ሲኾን፥ እነርሱም፡-
ü  በመጀመሪያ ሰዓተ ሌሊት - አራቱ ባሕርያተ ሥጋ እና ጨለማ፣
ü  ከኹለተኛው ሰዓተ ሌሊት እስከ ዘጠነኛው ሰዓተ ሌሊት - ከእሳት ሙቀቱን ትቶ ብርሃኑን ወስዶ ሰባቱ ሰማያትን፣
ü  በዘጠነኛው ሰዓተ ሌሊት ደግሞ መላእክትን ፈጠረ፡፡
እስኪ እያንዳንዳቸውን በመጠን በመጠኑ እንመልከታቸው፡፡

Monday, June 1, 2015

ትምህርተ ሃይማኖት (ክፍል አስር)

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ግንቦት 25 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ውድ የመቅረዝ አንባብያን! እንዴት ሰነበታችሁ? እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ዛሬም የትምህርተ ሃይማኖት ትምህርታችንን እንቀጥላለን፡፡ በዛሬው ክፍልም በክፍል ዘጠኝ የጀመርነውን የሥነ ፍጥረት ትምህርት ይኾናል፡፡ እግዚአብሔር ማስተዋሉን ጥበቡን ያድለን፡፡ አሜን!!!

Friday, May 29, 2015

አንዲት/አሐቲ/ ሰንበት ትምህርት ቤት



በዲ/ን ሕሊና በለጠ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ግንቦት 21 ቀን 2007 ዓ.ም.)፡-  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
አንድወይምአንዲትየሚለው ቃል በቤተ ክርስቲያናችን ከቁጥር መግለጫነቱ ባሻገር የጠለቀ ምሥጢራዊ ፍች ያለው ቃል ነው፡፡
ከምሥጢራት ሁሉ የረቀቀውን የሥላሴን ምሥጢር አባቶች ባስተማሩንና በተገለጠልን መጠን ስንገልጽ አንድምሦስትም መሆናቸውን እንመሰክራለን፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ የምናመልከው አምላክ በባሕሪየ መለኮቱ አንድ እንደሆነ መጽሐፍ ቅዱስአንድ ጌታበማለት ይጠቁመናል፡፡ በእርሷ መንገድነት ካልሆነ በቀር ጌታን ማግኘት አይቻልምና ይሄ አንድ ጌታ የሚገኝባትን ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስትና ሃይማኖትን መጽሐፍ ቅዱስአንድ ሃይማኖትሲል ይጠራታል፡፡ ያመነና የተጠመቀ ነውና የሚድነው /ማር.1616/ የድኅነት መንገድ ወደሆነችው ወደዚህች ሃይማኖት መግቢያ በር የሆነውን ምሥጢረ ጥምቀትንም በመቀጠልአንዲት ጥምቀትሲል ይገልጸዋል፡፡/ኤፌ.45/ ሐዋርያት ልቡናቸውና ቃላቸው በአንድነት የተባበረ ነውና በኤፌሶን መልእክቱ ቅዱስ ጳውሎስአንድያላትን ሃይማኖት ሐዋርያው ይሁዳምለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽማ የተሰጠችይላታል፡፡ /ይሁ. 3/

Wednesday, May 27, 2015

መቅረዝ ዘተዋሕዶ: በዓለ ጰራቅሊጦስ

መቅረዝ ዘተዋሕዶ: በዓለ ጰራቅሊጦስ: (መቅረዝ ዘተዋሕዶ፥ ግንቦት ፴ ቀን፥ ፳፻፮ ዓ.ም)፡ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!     “ጰራቅሊጦስ” ማለት በጽርዕ ልሳን “አጽናኝ” ማለት ነው፡፡ ምንም እንኳን በ፩ኛ ዮሐ.፪...

Sunday, May 24, 2015

አልማዝ - መድሎተ ጽድቅ



በዲ/ን ብርሃኑ አድማስ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
      “መድሎተ ጽድቅ - የእውነት ሚዛን” በሚል ርእስ ዲ/ን ያረጋል አበጋዝ ያዘጋጀው መጽሐፍ ግንቦት 8 ቀን 2007 ዓ.ም. ብጹዕ አቡነ ሉቃስ የሰቲት ሑመራ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ አበው ካህናት፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ ሰባክያነ ወንጌል እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ደማቅ መርሐ ግብር መመረቁ ይታወሳል፡፡ በዕለቱም ዲ/ን ብርሃኑ አድማስ የመጽሐፉን ዳሰሳ አቅርቦ ነበር፡፡ ዳሰሳው ካለው ዘርፈ ብዙ ጥቅም አንጻር እንደሚከተለው አቅርቤዋለሁ፡፡ መልካም ንባብ!!!

Wednesday, May 20, 2015

መቅረዝ ዘተዋሕዶ: ዕርገተ ክርስቶስ

መቅረዝ ዘተዋሕዶ: ዕርገተ ክርስቶስ: (መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ግንቦት ፳ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!! ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ከተነሣ በኋላ ዕለቱን ወደ ሰማይ አላ...

Monday, May 18, 2015

ይድረስ ለሯጩ ወንድሜ

በአሃ ገብርኤል
ከዓምደ ሃይማኖት /ሰ/ት/ቤት
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ግንቦት 11 ቀን 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
        ይድረስ ለወንድሜ ተስፋ እግዚአብሔር! እንደምን ሰንብተኻል? እኔ ቸሩ እግዚአብሔር ይመስገን ደኅና ነኝ፡፡ “በተመረቅኩት ሥራ ብዙ ዓመታት መሥራቴን ታውቃለኅ፡፡ አኹን ግን ትቼው አትሌት ኾኛለኁ፡፡ ለመኾኑ ሯጭነት ኃጢአት ነውን?” ብለኽ የጻፍክልኝ ደብዳቤ ደርሶኛል፡፡
        ውድ ወንድሜ! ሩጫችን ይለያያል እንጂ ኹላችንም ሯጮች ነን፡፡ በርግጥ የሚገባና የማይገባ ሩጫ እንዳለ ልትዘነጋ አይገባም፡፡ ጥያቄኽ የኹላችንም ጥያቄ በመኾኑ የጥያቄአችን መልስ የሚኾነን ደግሞ ቃለ እግዚአብሔር ነው፡፡ ታስታውስ እንደኾነ የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት ከኾንን በኋላ በጕባኤ “ታገኙ ዘንድ ሩጡ” /1ኛ ቆሮ.9፡24/ በሚል ርእስ ተምረን ነበር፡፡ ዛሬ አንተ ሯጭ ኾነህ በምሳሌ የተማርነውን በተግባር እያስታወስከው እንድትማርበት ዕድሉን በማግኘትህ ደስ ልትሰኝ ይገባኻል፡፡

Thursday, May 14, 2015

በፊቴም እረዱአቸው /ሉቃ.19፡27/



በዲ/ን ዶ/ር ቴዎድሮስ በለጠ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ግንቦት 6 ቀን 2007 ዓ.ም.)፡-  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ስመ እግዚአብሔር ቀዳማዊ ዘእንበለ ትማልም፤ ወማዕከላዊ ዘእንበለ ዮም፤ ወደኃራዊ ዘእንበለ ጌሰም ፤ብሉየ መዋዕል ዘእንበለ ዓም፤ ፈጣሬ ኩሉ ዓለም ዘእንበለ ድካም፤ ባህረ ምሕረት ዘእንበለ አቅም፤ ብኁተ ሕሉና እስከ ለዓለመ ዓለም አሜን::
"ወባህቱ ለእልክቱሰ ጸላእትየ እለ ኢይፈቅዱ እንግሥ ላእሌሆሙ አምጽእዎሙ ዝየ ወርግዝዎሙ በቅድሜየ= ነገር ግን እነዚያን በላያቸው ልነግሥ ያልወደዱትን ጠላቶቼን ወደዚህ አምጡአቸው ።" ሉቃ.19:27

Tuesday, May 12, 2015

“ከካህናት ጋር አብሬ ስለማገለግል ንስሐ መግባት ከበደኝ፡፡ ምን ላድርግ?”



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ማግሰኞ ግንቦት 4 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ውድ መቅረዛውያን እንዴት አላችኁ? ዛሬም ከአንባብያን ከተላኩልኝ ጥያቄዎች መካከል አንዱን መርጬ በአበው ካህናት የተሰጠውን ምላሽ ይዤላችኁ ቀርቢያለኁ፡፡ ዛሬም መልሱን የሚሰጡን በምሥራቀ ፀሐይ ቀበና መድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን ሰባኬ ወንጌል እንዲኹም በታዕካ ነገሥት ባዕታ ለማርያም ገዳም የመጻሕፍተ ሐዲሳት የ5ኛ ዓመት ደቀ መዝሙርና የዘንድሮ ተመራቂ የኾኑት ቀሲስ ፋሲል ታደሰ ናቸው፡፡ ለአባታችን ተናጋሪ አንደበት ለእኛም ሰሚ እዝነ ልቡና ያድለን፡፡ አሜን!!!
ጥያቄ፡-  “ውድ መቅረዞች! እንዴት አላችኁ? የመቅረዝ አንባቢ ነኝ፡፡ ከምእመናን የምታስተናግዱት ጥያቄ በጣም ጥሩ ነው፡፡ እኔም ከንስሐ አባት ጋር የተያያዘ ጥያቄ አለኝ፡፡ እኔ በምኖርበት አከባቢ ከካህናት ጋር አብሮ የመሥራትና የመቀራረብ ነገር አለ፡፡ ይኽም ለእኔ ብቻ ሳይኾን የሀገሩ ጠባይ የፈጠረው ነው፡፡ እናማ ባለን ቅርርብ በቤተ ክርስቲያን ጕዳይ አለመግባባት ሲፈጠርም ኾነ በሌላ ጕዳይ በአካልም ኾነ በስልክ እንደ ልብ ስለምናወራ የሰው ስም እያነሣን ስናማ፣ ስናወግዝ አብረን ስለምንውል እንዴት መናዘዝ እችላለኁ?”
አንዳርግ ነኝ ከቺካጎ

Saturday, May 2, 2015

ለክርስትና ሃይማኖት ግድ ያለው ሰው ኹሉ ሊያነበው የሚገባ መጽሐፍ!



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ 24 ቀን 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
በዲያቆን ያረጋል አበጋዝ የተዘጋጀውና “መድሎተ ጽድቅ (የእውነት ሚዛን)” የተሰኘው ድንቅ መጽሐፍ በገበያ ላይ ዋለ፡፡
ይኽ መጽሐፍ ራሳቸውን “ተሐድሶ” ብለው የሚጠሩት አካላት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን እምነትና ትምህርትን በተመለከተ በሐሰትና በስሕተት ላሠራጯቸው የስሕተት ትምህርቶች መልስ የሚሰጥ ድንቅ መጽሐፍ ሲኾን በአንጻሩም መጽሐፍ ቅዱሳዊና ሐዋርያዊ የኾነው የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ትምህርት በጥልቀትና በስፋት የቀረበበት መጽሐፍ ነው፡፡ በውስጡም፡-

Thursday, April 30, 2015

ስለ ጌጠኛ ልብስ

በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ 22 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ዕርቃናችንን የምንሸፍንበት ልብስ ብቻ ልንለብስ ይገባናል፡፡ ብዙ ወርቅን ብናደርግ ምንድነው ትርጉሙ? ብዙ ወርቅን ማድረግ በተውኔት ቤት ነው፤ ተዋንያን ብዙ ተመልካችን ለማግኘት ያደርጉታልና፡፡ ጌጠኛ ልብስ መልበስ የአመንዝራ ሴቶች ግብር ነው፤ ብዙ ወንዶች ይመለከቷቸው ዘንድ ይኽን ያደርጋሉና፡፡ እነዚኽን ማድረግ ልታይ ልታይ ለሚሉ ሰዎች ነው፡፡ እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት የምትሻ ሴት ግን ይኽን ጌጥ ማድረግ አትፈልግም፡፡ ራሷን የምታስጌጠው በሌላ መንገድ ነው፡፡ እናንተም ይኽን ጌጥ ማድረግ የምትፈልጉ ከኾነ ማድረግ ትችላላችኁ፡፡ ተውኔት ቤትን የምትሹ ከኾነም ወርቀ ዘቦአችኁን የምታደርጉበት ሌላ ተውኔት ቤት አለላችኁ፡፡ ያ ተውኔት ቤትስ ምንድነው? መንግሥተ ሰማያት ነው፡፡ ተመልካቾቹ ቅዱሳን መላእክት ናቸው፡፡ ይኽን የምናገረው በገዳም ለሚኖሩት መኖኮሳይያት ብቻ አይደለም፤ በማዕከለ ዓለም ለሚኖሩትም ኹሉ ጭምር እንጂ፡፡ በክርስቶስ ክርስቲያን በወልድ ውሉድ የተባለ ኹሉ የራሱ ተውኔት ቤት አለው፡፡ ስለዚኽ ተመልካቾቻችንን ደስ ለማሰኘት ራሳችንን ደኅና አድርገን እናጊጥ ብዬ እማልዳችኋለኁ፡፡ ለመድረኩ የሚመጥን ልብስን እንልበስ፡፡ እስኪ ንገሩኝ! አንዲት ሴሰኛ ሴት ተውኔት ለመሥራት ብላ ብዙ ወርቋን አወላልቃ፣ ቄንጠኛ መጎናጸፍያዋን ጥላ፣ በሳቅ በስላቅ ሳይኾን ቁም ነገርን ይዛ፣ ተርታ ልብስን ለብሳ ወደ መድረኩ ብትወጣና ሃይማኖታዊ ንግግርን ብትናገር፣ ስለ ንጽሕና ስለ ቅድስና ብትናገር፣ ሌላ ክፉ ንግግርም ባትጨምር በተውኔት ቤቱ የሞላው ሰው አይነሣምን? ተመልካቹ ኹሉ የሚበተን አይደለምን? ሰይጣን የሰበሰበው ተመልካቹ የማይፈልገውን ነገር ይዛ ስለ መጣች ኹሉም የሚሳለቅባትና እንደ ትልቅ አጀንዳ የሚወራላት አይደለምን? አንተም በብዙ ወርቅ፣ በጌጠኛ ልብስ ተሸላልመኽ ወደ መንግሥተ ሰማያት ብትገባ ቅዱሳን መላእክት አስወጥተው ይሰዱኻል፡፡ ምክንያቱም በመንግሥተ ሰማያት የሚያስፈልገው ልብስ እንደዚኽ ዓይነት አይደለም፤ ሌላ ነው እንጂ፡፡ “ርሱስ ምን ዓይነት ነው?” ትለኝ እንደኾነም “ነፍስን በትሩፋት ማስጌጥ ነው” ብዬ እመልስልኻለኁ፡፡ ነቢየ እግዚአብሔር ክቡር ዳዊት፡- “ልብሷ የወርቅ መጐናጸፍያ ነው” ያለውም ይኽንኑ ነው እንጂ በዚኽ ምድር የምንለብሰው ልብሳችንን ፀዓዳና አንጸባራቂ ስለ መኾን አይደለም /መዝ.45፡13/፡፡ ምክንያቱም “ለሐሴቦን ንጉሥ ልጅ ኹሉ ክብሯ ነው” እንዳለ በዚያ (በመንግሥተ ሰማያት) መራሔ ተውኔቷ ርሷ ናት፡፡ እኅቴ ሆይ! ራስሽን መሸላለም ብትፈልጊ እንዲኽ አጊጪ፡፡ ከዚያም ከምረረ ገሃነም ትድኛለሽ፡፡ ባልሽንም ከማዘን ከመቆርቆር ትታደጊዋለሽ፡፡

Tuesday, April 28, 2015

የጉባኤ ጥሪ ከዓምደ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት

“ተዋሕዶ ሃይማኖታችን፣ ቤተ ክርስቲያን እናታችን” በማለታቸው በዓለማቀፉ አሸባሪ ቡድን በአይሲስ የተገደሉት ኢትዮጵያውያን ሰማዕታትን ለማሰብ የመንበረ መንግሥት (ግቢ) ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ዓምደ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት ሚያዝያ 23 ቀን 2007 ዓ.ም. ልዩ መንፈሳዊ ጉባኤ አዘጋጅቷል፡፡ በዕለቱ “ሰማዕትነት በዘመናችን” በሚል ዐቢይ ርእስ የምክክር ጉባኤ የሚደረግ ሲኾን ሚያዝያ 20፣ 21፣ እና 22 ቀን 2007 ዓ.ም. ለሦስት ተከታታይ ቀናት ከቀኑ 12፡00 ሰዓት ዠምሮ የጸሎት መርሐ ግብር ይካሔዳል፡፡

የመስቀሉ ሕዝቦች

      (መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ 20 ቀን 2007 ዓ.ም.)፡-በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
 በቅርቡ አይሲስ  የተባለው “ሃይማኖታዊ” ድርጅት “ክርስቲያን መግደል ገነት ያስገባል ፤ አላህ ደማቸውን እያየ ደስ ይለዋል” በሚል እንኳን መንፈሳዊነት ሰብአዊነት በጎደለው ፍፁም ሰይጣናዊ ትምህርት መነሻ በማድረግ ምንም የማያውቁትን ምስኪኖች በጭካኔ ግማሹን በተማሩት ትምህርት እንደበግ እያረዱ ግማሹን ደግሞ በጥይት እያርከፈከፉ ፈጅተዋቸዋል፡፡ በዚህም የኦርቶዶክሳውያን ልብ ፍፁም አዝኗል፤ አልቅሷል፡፡
ይሁን እንጂ ‹‹ መሳ ፲፬፡ ፰ - ፲፬ ከበላተኛው መብልን የሚያወጣ ››ጌታ ከእነዚህ አረመኔዎች አንድ አስደናቂ ቃል አሰምቶናል፡፡ ይኸውም እነዚህ አረመኔዎች ምስኪኖቹን ኦርቶዶክሳውያን ከማረዳቸው በፊት ሁሉንም በወል የጠሩበት ስም ‹‹ የመስቀሉ ሕዝቦች ›› የሚል ነው፡፡ መጽሐፍ  በ‹‹ዮሐ ፲፩ ፤ ፵፱ በዚያችም አመት የካህናት አለቃ የነበረው ስሙ ቀያፋ የተባለው ከእነርሱ አንዱ እንዲህ አላቸው ‹ እናንተስ ምንም አታውቁም ፤ ምንም አትመክሩም ሕዝቡ ሁሉ ከሚጠፋ  ስለ ሕዝቡ አንድ ሰው ቢሞት ይሻለናልና ›፡፡ ይህንም ከልቡ የተናገረ አይደለም ፤ ነገር ግን በዚያች አመት የካህናት አለቃ ነበርና ጌታችን ኢየሱስ ስለ ሕዝቡ ይሞት ዘንድ ስላለው ይህን ትንቢት ተናገረ፡፡››  እንደሚል ቀያፋን ክርስቶስ ለሰው ዘር በሙሉ በፈቃዱ ይሞት ዘንድ እንዳለው ትንቢት ይናገር ዘንድ ያደረገ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ፤ ዛሬም እነዚህን አረመኔዎች አፋቸውን ከፍቶ ፊታቸውን ጸፍቶ ስለ ኦርቶዶክሳውያን ያስመሰከራቸው ቃል እንጂ ወደው አስበው የተናገሩት አይደለም፡፡ ለዚህም አንዳንድ ማሳያዎችን ላቅርብ፡፡

Saturday, April 25, 2015

ሰማዕታት

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ 17 ቀን 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
        ሰማዕት የሚለው ቃል ስርወ ቃሉ “ሰምዐ” የሚል ሲኾን ይኸውም ሰማ፣ አደመጠ፣ አስተዋለ፣ ተቀበለ፣ መሰከረ፣ ምስክር ኾነ፣ ያየውን የሰማውን ተናገረ፤ አየኹ ሰማኹ አለ ማለት ነው፡፡ በመኾኑም ሰማዕት ማለት የሚመሰክሩ፣ ሃይማኖታቸውን መስክረው በሰማዕትነት የሚሞቱ ማለት ነው፡፡ ለአንድ ሰማዒ ሲኾን ሲበዛ ሰማዕት ይኾናል፡፡
በቤተ ክርስቲያን ታሪክ የሰማዕታት መዠመሪያ የሚባለው አቤል ነው፡፡ በአክአብና በኤልዛቤል ትእዛዝ በድንጋይ ተወግሮ በግፍ የተገደለው ናቡቴ፣ በይሁዳ ንጉሥ በምናሴ ትእዛዝ በእግሮቹና በራሱ መካከል በመጋዝ ተሰንጥቆ የሞተው ነቢዩ ኢሳይያስ፣ እንዲኹም በአይሁድ በድንጋይ ተወግሮ የተሠዋው ነቢዩ ኤርምያስም ተጠቃሾች ናቸው፡፡
በዘመነ ሐዲስም ከሕፃናተ ቤተ ልሔም የዠመረው በእነ ካህኑ ዘካርያስ፣ መጥምቁ ዮሐንስ፣ ቅዱስ ጴጥሮስ፣ ቅዱስ ጳውሎስ፣ ቅዱስ እስጢፋኖስ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ቅዱስ መርቆሬዎስ፣ ቅዱስ ቂርቆስ፣ በአጠቃላይ በዲዮቅልጥያኖስና መክስምያኖስ የተጨፈጨፉት የሦስተኛውና የአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ሰማዕታት በዋናነት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡
በኢትዮጵያም ሰማዕትነትና ክርስትና የአንድ ሳንቲም ኹለት ገጽታዎች ናቸው፡፡ ዮዲት ጉዲት፣ ግራኝ አሕመድ፣ ሱስንዮስ፣ ፋሺስት ጣልያን፣ ደርግ፣ እንዲኹም በቅርቡ በአርሲ በምዕራብ ሐረርጌ በጅማ አጋሮ በአክራሪ ሙስሊሞች የተፈጸሙት ለዚኽ ማሳያዎች ናቸው፡፡
ከዚኽ በመቀጠል ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ “The Cult of the Saints - ፍኖተ ቅዱሳን” በተሰኘ መጽሐፍ በጊዜው ለነበሩ ምእመናን ስለ ተለያዩ ሰማዕታት ያስተማራቸውን ትምህርት ከአኹኑ ኢትዮጵያውያን ሰማዕታት ጋር እያገናዘብኩ የተረጐምኩትን በአጭሩ አቅርቤላችኋለኁ፡፡ መልካም ንባብ፡፡

Thursday, April 23, 2015

ሰው ሲሞትብን ምን እናድርግ?

በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ 15 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

ልጆቼ! ክርስቲያን ሲያርፍ አግባብ የሌለው ለቅሶ አይለቀስም፡፡ ታላቅ የኾነ ሥነ ሥርዓት እየተካሔደ ሳለ ለቅሶ አይለቀስም፡፡ እማልዳችኋለሁ! እስኪ ልጠይቃችሁና እናንተም መልሱልኝ! ኹላችንም በአንድ ቦታ ተሰብሰበን ሳለ የሀገራችን ንጉሥ ለአንዳችን የጥሪ ወረቀት ልከው ለእራት ግብዣ ጠሩን እንበል፡፡ ከእኛ መካከል ወደ ንጉሡ ተጠርቶ ስለ ሔደው ሰው የሚያለቅስ ማን ነው?

Wednesday, April 15, 2015

መንፈሳዊ ሕይወት ከትንሣኤ እስከ ጰራቅሊጦስ

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ 8 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
(ይኽ ጽሑፍ ከዚኽ በፊት ተለጥፎ የነበረ ነው)
        በቤተ ክርስቲያናችን ሥርዓት መሠረት ከትንሣኤ እስከ ጰራቅሊጦስ እሑድ ባለው ወራት ረቡዕንና ዓርብን ጨምሮ አይጦምም፤ የቀኖና ስግደትም አይሰገድም፡፡ ይኽም ሠለስቱ ምዕት በ325 ዓ.ም. በጉባኤ ኒቅያ ሲሰበሰቡ በሀያኛው ቀኖኗቸው የወሰኑት ቀኖና ነው /ሃይ.አበ.20፡26፣ The Oxford Dictionary of the Christian Church, pp 1250, 1738/፡፡ ይኽን ቀኖና ሲወስኑም ያለ ምክንያት አይደለም፡፡ ይኽ ወራት ከትንሣኤ ዘጉባኤ በኋላ ያለውን ሕይወታችን የሚያሳይ ስለኾነ ነው እንጂ፡፡ ከትንሣኤ ዘጉባኤ በኋላ ፈቃደ ሥጋን ለፈቃደ ነፍስ ለማስገዛት ተብሎ የሚደረግ ጦምም ኾነ ስግደት የለም፡፡ ሰውነታችን ሙሉ በሙሉ በዲያብሎስ ከመፈተን፣ ከእግዚአብሔር ውጪ የኾነ ሌላ ሐሳብን ከማሰብ ነጻ የሚወጣበት ወራት ነው፡፡ በዚያ ሰዓት ፈቃዳችን ከፈቃደ እግዚአብሔር ጋር የተስማማ ነው፡፡ ሥጋ ሙሉ ለሙሉ ከድካሙ ነጻ ስለሚኾን እግዚአብሔርን ለማመስገን ትጉኅ ነው፡፡ እንደ አኹኑ እንቅልፍ እንቅልፍ አይለውም፤ ዘወትር የቅዱሳን መላእክትን ምግብ ለመብላት ማለትም ለማመስገን የተዘጋጀ ነው እንጂ፡፡

Monday, April 13, 2015

ትምህርተ ሃይማኖት (ክፍል ዘጠኝ)

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ 6 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
        ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን - በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን
        አሰሮ ለሰይጣን - አግዐዞ ለአዳም
        ሰላም - እምእዜሰ
        ኮነ - ፍሰሐ ወሰላም
        ውድ የመቅረዝ አንባብያን! እንዴት አላችኁ? የትምህርተ ሃይማኖት ትምህርቱን እየተከታተላችኁ እንደኾነ ጽኑ እምነቴ ነው፡፡ እስከ አኹን ድረስ የትምህርተ ሃይማኖት መግቢያ፣ የሃይማኖት አዠማመርና እድገት፣ ከኹሉም በፊት አንድ ኦርቶዶክሳዊ ክርስቲያን ማወቅ ያለበት ብለን ነገረ ቤተ ክርስቲያን፣ ቅዱስ ትውፊት፣ ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ አረዳድ፣ ስለ ዶግማና ቀኖና፤ ስለ እግዚአብሔር መኖርና ስለ ባሕርዩ ጠባያት እንዲኹም ስሙ ማን እንደኾነ ተማምረናል፡፡ ዛሬም ሥነ ፍጥረት ብለን እንቀጥላለን፡፡ እግዚአብሔር ማስተዋልን ያድለን፡፡ አሜን!!!

Saturday, April 11, 2015

መቅረዝ ዘተዋሕዶ: በዓለ ትንሣኤ

መቅረዝ ዘተዋሕዶ: በዓለ ትንሣኤ: በገብረ እግዚአብሔር (መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሚያዝያ ፲፩ ቀን፣ ፳፻፮ ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!! የዚኽ ትምህርት መሠረታዊ ዓላማ ክርስቲያኖች ክርስቶስን መስለው ...

Tuesday, April 7, 2015

በአስቆሮቱ ይሁዳ ዙርያ የሚነሡ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 30 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
        ጌታችንን አሳልፎ የሰጠው ከዐሥራ ኹለቱ ሐዋርያት የነበረው የአስቆሮቱ ይሁዳ ነው፡፡ አስቆሮት በይሁዳ አውራጃ የሚገኝ ቂርያትሐጾር የሚባል መንደር ነው /ኢያሱ.15፡25/፡፡ የሐዋርያት ገንዘብ ያዥ ኾኖ ሳለ ለራሱ ገንዘብ ይሰርቅ ነበር፡፡ በኋላም ስለ ገንዘብ ጌታችንን አሳልፎ ለመስጠት ተስማምቷል፡፡ ብዙ ሰዎች በይሁዳ ዙርያ የተለያዩ ጥያቄዎችን ያነሣሉና ለዚኽ መልስ ይኾነን ዘንድ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የማቴዎስ ወንጌልን በተረጐመበት 81ኛው ድርሳኑ ላይ የተናገረውን ወደ አማርኛ መልሼ አቅርቤላችኋለኁ፡፡ መልካም ንባብ!!!

Thursday, April 2, 2015

በፌስ ቡክ የምጽፈውና የእኔ ማንነት አይገናኝም፡፡ ምን ላድርግ?



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐሙስ መጋቢት 24 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ውድ መቅረዛውያን እንዴት አላችኁ? ዛሬም ከአንባብያን ከተላኩልኝ ጥያቄዎች ለሦስተኛው ጥያቄ የተሰጠውን ምላሽ አቀርብላችኋለኁ፡፡ መልሱን የሚሰጡን በምሥራቀ ፀሐይ ቀበና መድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን ሰባኬ ወንጌል እንዲኹም በታዕካ ነገሥት ባዕታ ለማርያም ገዳም የመጻሕፍተ ሐዲሳት የ5ኛ ዓመት ደቀ መዝሙርና የዘንድሮ ተመራቂ የኾኑት ቀሲስ ፋሲል ታደሰ ናቸው፡፡ የልድያን ልቡና የከፈተ አምላክ የእኛንም እዝነ ልቡናችን ይክፈትልን፡፡ አሜን!!!

Monday, March 30, 2015

ትምህርተ ሃይማኖት - ክፍል ስምንት

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐሙስ መጋቢት 22 ቀን 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
        ውድ የመቅረዝ ተከታታዮች! እንዴት አላችኁ? ባለፉት ሰባት ተከታታይ ትምህርቶች ስለ መሠረታዊው ትምህርተ ክርስትና ደኅና አድርገን ለመማማር ሞክረናል፡፡ እግዚአብሔር ፈቃዱ ኾኖ ዛሬም በዚኽ ክፍል ተገናኝተናል፡፡ እግዚአብሔርም ያስተምረናል፡፡

Thursday, March 26, 2015

ኃጢአቴን በዝርዝር አለመናዘዜ አስጨነቀኝ፡፡ ምን ላድርግ?



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐሙስ መጋቢት 17 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ውድ መቅረዛውያን እንዴት አላችኁ? በዛሬው ጽሑፌ ከአንባብያን ከተላኩልኝ ጥያቄዎች ለኹለተኛው ጥያቄ የተሰጠውን ምላሽ አቀርብላችኋለኁ፡፡ መልሱን የሚሰጡን በምሥራቀ ፀሐይ ቀበና መድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን ሰባኬ ወንጌል እንዲኹም በታዕካ ነገሥት ባዕታ ለማርያም ገዳም የመጻሕፍተ ሐዲሳት የ5ኛ ዓመት ደቀ መዝሙር የኾኑት ቀሲስ ፋሲል ታደሰ ናቸው፡፡ የልድያን ልቡና የከፈተ አምላክ የእኛንም እዝነ ልቡናችን ይክፈትልን፡፡ አሜን!

ጥያቄ፡- ሰላም ለእናንተ ይኹን መቅረዞች!!! አንድ ውስጤን የሚያስጨንቀኝና እንቅልፍ ያሳጣኝ ጥያቄ አለኝ፡፡ ለብዙ ዓመታት እምነቴ ፕሮቴስታንት ነበር፡፡ እ.ኤ.አ. 2010 ላይ ግን ወደ ኦርቶዶክስ ተመልሻለኁ፡፡ ከንስሐ አባቴ ጋርም ተገናኝቻለኁ፡፡ ነገር ግን ኃጢአቴን ስናዘዝ በደፈናው “ከመግደል ውጪ ኹሉንም ሠርቻለኁ” ነው ያልኳቸው፡፡ አኹን ግን “ለምን ኹሉንም በዝርዝር አልነገርኳቸውም? በግልጽ ባለ መናገሬ እግዚአብሔር ይቅር ባይለኝስ? እንዴትስ በድጋሜ ልንገርዎት ልበላቸው?” እያልኩ ቀን በቀን እጨነቃለኁ፡፡ ምን እንዳደርግ ትመክሩኛላችኁ? 
ሳምራዊት ነኝ ከሆላንድ

Tuesday, March 24, 2015

የመስጠትና የመቀበል ስሌት




በዲ/ን ብርሃኑ አድማስ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ማግሰኞ መጋቢት 15 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
        ውድ የመቅረዝ ዘተዋሕዶ አንባብያን እንዴት አላችኁ? ይኽ ዛሬ የምናቀርብላችኁ ጽሑፍ ዲ/ን ብርሃኑ አድማስ ማኅበረ ቅዱሳን መጋቢት 13 ቀን 2007 ዓ.ም. በኦሎንኮሚ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ባዘጋጀው 8ኛው የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር ላይ የሰበከው ስብከት ነው፡፡ ስብከቱ 44 ደቂቃን የፈጀ በመኾኑ ወደ ጽሑፍ ሲቀየር ትንሽ ረዘም ይላል፡፡ ነገር ግን የሐሳቡ ፍሰት እንዳይቆራረጥ ብዬ በክፍል በክፍል ላቀርበው አልመረጥኩም፡፡ ከዚኽም በተጨማሪ በስብከቱ ውስጥ የሚደጋገሙ ዐረፍተ ነገሮችንና በጉባኤው ላለ ሰው ካልኾነ በቀር ለአንባቢ የማይረዱ ጥቃቅን ሐሳቦችን ከማውጣት ውጪ ምንም የቀነስኩትም የጨመርኩትም ነገር የለም፡፡ ስለ ኹሉም መልካም ንባብ ይኹንላችኁ!!!

Wednesday, March 18, 2015

በተመሳሳይ ኃጢአት እየወደቅኩ ተቸገርኩኝ፡፡ ምን ላድርግ?

(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ሐሙስ መጋቢት 10 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሑደ አምላክ አሜን!!!
        ውድ መቅረዛውያን እንዴት አላችኁ? በዛሬው ጽሑፋችን ከአንባብያን ከተላኩልን ጥያቄዎች አንዱን ካህናትን ጠይቀን መልስ ይዘን መጥተናል፡፡ መልሱን የሚሰጡን በምሥራቀ ፀሐይ ቀበና መድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን ሰባኬ ወንጌል እንዲኹም በታዕካ ነገሥት ባዕታ ለማርያም ገዳም የመጻሕፍተ ሐዲሳት የ5ኛ ዓመት ደቀ መዝሙር የኾኑት ቀሲስ ፋሲል ታደሰ ናቸው፡፡ ለርሳቸው ተናጋሪ አንደበት ለእኛም ሰሚ እዝነ ልቡና ያድለን፡፡ አሜን!!!
ጥያቄ፡- “እንደምን አላችኁ መቅረዞች? እባካችሁ አንድ ኃጢአት በተደጋጋሚ እሠራለሁ፡፡ ንስሐ አባቴ ጋር በተደጋጋሚ ብሔድም ኃጢአቴን መተው አልቻልኩም፡፡ ምን ላድርግ? እባካችሁ ጉልበት የሚኾነኝ ምክር ስጡኝ፡፡ እግዚአብሔር ይስጥልኝ፡፡”

Monday, March 16, 2015

ወደ እግዚአብሔር ለመድረስ (ደረጃ አራት)





በዲ/ን ሳምሶን ወርቁ
(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ማክሰኞ መጋቢት 8 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
መታዘዝ
የተከበራችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች፥ የመንግሥተ እግዚአብሔር ተጓዦች እንዴት ሰነበታችሁ? አራተኛውን የመንፈሳዊ ሕይወት ደረጃ እነሆ በምናባችን ዛሬ መመልከታንን እንቀጥላለን፡፡ አስቀድመን የመጀመሪያውን የመንፈሳዊ ሕይወት ደረጃ ጀርባችን ለዓለም በመስጠት ጀምረን፣ ሁለተኛውን የመንፈሳዊ ሕይወት ደረጃ ከዓለማዊ መሻት መለየትን አስከትለን፣ በሦስተኛው የመንፈሳዊ ሕይወት ደረጃ የሆነውን እንደ እንግዳ መኖርን በባለፉት ጊዜያት ተመልክተናል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ዘላዕለይ አራተኛውን የመንፈሳዊ ሕይወት ደረጃ መታዘዝ ሲል ይገልጸዋል፡፡ ይህንንም ሲገልጽ መታዘዝ ማለት የእኔ የምንለውን ሐሳብ፣ ፈቃድ በመተው በምትኩ እኛ ራሳችንን አስገዝተንለታል ለምንለው ለእግዚአብሔር ፈቃድ በመታዘዝ መኖር ማለት ነው፡፡

Thursday, March 12, 2015

አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ መጋቢት 03 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
     በየዓመቱ መጋቢት 5 የምናከብረው በዓል አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ያረፉበት በዓል ነው፡፡ በዚኽ ዕለት ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በቅዳሴዋም በትምህርቷም ኹሉ እኒኽን ታላቅና ቅዱስ አባት ታነሣለች፤ ታወድሳለች፤ ተጋድሎአቸውንም ለልጆቿ ታስተምራለች፡፡
ሀገራቸው ንሒሳ (ግብጽ) ሲኾን አባታቸው ስምዖን እናታቸውም አቅሌስያ ይባላሉ፡፡ ልጅ አጥተው 30 ዓመታት ሲያዝኑ ኖረዋል፡፡ እኛ አንድ ነገርን ለምነን በእኛ አቈጣጠር ካልተመለሰልን ስንት ቀን እንታገሥ ይኾን? ዛሬ በልጅ ምክንያት የፈረሱ ትዳሮች ስንት ናቸው? ለመኾኑ እግዚአብሔርን ስንለምነው እንደምን ባለ ልቡና ነው? ጥያቄአችን ፈጥኖ ላይመለስ ይችላል፡፡ ያልተመለሰው ለምንድነው ብለን ግን መጠየቅ ይገባናል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፡- “የምንለምነውን የማናገኘው በእምነት ስለማንለምን ነው፤ በእምነት ብንለምንም ፈጥነን ተስፋ ስለምንቆርጥ ነው” ይላል፡፡ ሰውን ብንለምነው እንደዘበዘብነው፣ እንደ ጨቀጨቅነው አድርጎ ሊቈጥረው ይችላል፡፡ እግዚአብሔር ግን እንዲኽ አይደለም፡፡ “ለምኑ ታገኙማላችሁ፤ አንኳኩ ይከፈትላችሁማል” ያለን ርሱ እግዚአብሔር እንጂ ሰው አይደለምና፡፡ የሚያስፈልገን ከኾነ ያለ ጥርጥር ይሰጠናል፡፡ መቼ? ዛሬ ሊኾን ይችላል፤ ነገ ሊኾን ይችላል፤ ወይም እንደ ስምዖንና እንደ አቅሌስያ የዛሬ 30 ዓመት ሊኾን ይችላል፡፡  ጭራሽኑ ላይሰጠንም ይችላል፡፡ አልሰጠንም ማለት ግን ጸሎታችን ምላሽ አላገኘም ማለት አይደለም፡፡ የለመንነው እኛን የሚጎዳን ስለኾነ እንጂ፡፡ እግዚአብሔር ሲሰጥ ስለ ፍቅሩ፤ ሲነሳም ስለ ፍቅሩ ነውና፡፡

Tuesday, March 10, 2015

ኹለት መንፈሳውያን መጻሕፍት ተመረቁ



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ረቡዕ 02 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- “ሰማዕትነት አያምልጣችሁ” እና “ነጽሮተ ሀገር” በሚል ርእስ የተዘጋጁ ኹለት መንፈሳውያን መጻሕፍት የካቲት 28 ቀን 2007 ዓ.ም. በገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ጥሪ የተደረገላቸው አበው ካህናት፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ ሰባክያነ ወንጌል እና የመቅረዝ ዘተዋሕዶ ድረ ገጽ አንባብያን በአጠቃላይ ከ400 በላይ ታዳምያን በተገኙበት ደማቅ መርሐ ግብር ተመረቁ፡፡ “ሰማዕትነት አያምልጣችሁ” የሚል ርእስ የተሰጠው አንደኛው መጽሐፍ በመቅረዝ ዘተዋሕዶ ድረ ገጽ ዋና አዘጋጅ በገ/እግዚአብሔር ኪደ የተተረጐመ የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሥራ ሲኾን ኹለተኛው መጽሐፍ ደግሞ በመምህር ዘሪኹን መንግሥቱ የተዘጋጀ መጽሐፍ ነው፡፡ መርሐ ግብሩ በአባ አሥራተ ማርያም ደስታ በጸሎት የተከፈተ ሲኾን ዘማሪት ጽጌ ወቅቱን የተመለከተ ያሬዳዊ መዝሙር አቀረበች፡፡

Wednesday, March 4, 2015

በመጽሐፍ ምረቃ ቀን እንዲገኙ ተጋብዘዋል



(መቅረዝ ዘተዋሕዶ፣ ረቡዕ የካቲት 28 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.)፡- በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
     ሰላመ እግዚአብሔር ይብዛላችሁ ውድ የመቅረዝ አንባብያን፡፡ እንደምን ሰነበታችሁ? እግዚአብሔር ቢወድና ቢፈቅድ ቀጣይ ቅዳሜ ማለትም የካቲት 28 ቀን 2007 ዓ.ም. በገ/ጽ/ቅ/ጊ/ቤተ ክርስቲያን (ፒያሳ) ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ዠምሮ ኹለት መጻሕፍት አንድ ላይ ይመረቃሉ፡፡ አንደኛው መጽሐፍ በገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተተረጎመው የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ መጽሐፍ ሲኾን ኹለተኛው መጽሐፍ ደግሞ የዓምደ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት የትምህርት ክፍል ሰብሳቢ በኾኑት በመምህር ዘሪኹን መንግሥቱ የተዘጋጀ ነው፡፡

FeedBurner FeedCount